Лента постов канала Dire-Dawa University (@DDUniv) https://t.me/DDUniv An Official Channel of Dire-Dawa University ru https://linkbaza.com/catalog/-1001353914659 Tue, 19 Aug 2025 18:09:23 +0300
Подробнее
]]>
https://linkbaza.com/catalog/-1001353914659 Fri, 15 Aug 2025 21:57:43 +0300
Подробнее
]]>
https://linkbaza.com/catalog/-1001353914659 Thu, 14 Aug 2025 17:07:43 +0300
Подробнее
]]>
https://linkbaza.com/catalog/-1001353914659 Wed, 13 Aug 2025 19:58:13 +0300
Подробнее
]]>
https://linkbaza.com/catalog/-1001353914659 Wed, 13 Aug 2025 19:06:20 +0300
Подробнее
]]>
https://linkbaza.com/catalog/-1001353914659 Tue, 12 Aug 2025 19:17:22 +0300
የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በ2018 ዓ/ም የትምህርት ዘመን ሞዴል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለማቋቋም ዝግጅት ማጠናቀቁን አስታወቀ።
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ9ኛ ክፍል ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር የሚጀምር ሞዴል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለማቋቋም የመጨረሻ የዝግጅት ምእራፍ ላይ መሆኑን አስታውቋል።

የሚቋቋመው ሞዴል ትምህረት ቤት ዩኒቨርሲቲው በዚሁ ጉዳይ ልይ የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት ቢሮ ከፍተኛ አመራሮች የመከሩ ሲሆን ለትምህርት ቤቱ መቋቋም የሚያስፈልጉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ላይ ትኩረት ያደረገ ፍሬያማ ውይይት አካሂደዋል።

የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ምርምር እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ተማም አወል በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት "የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ከማስተማርና ምርምር ጎን ለጎን የማኅበረሰብ አገልግሎት ስራዎችን ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ ጠቁመው አዲስ የሚከፈተው ሞዴል ትምህርት ቤት ዩኒቨርሲቲው በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ እየሰራ ያለውን ሰፊ ስራ የሚያሳይ ነው’’ ብለዋል።

የሚቋቋመው ሞዴል ትምህርት ቤት ብቁና ተወዳዳሪ ዜጎችን ከታች ጀምሮ ለማፍራት ያለንን ቁርጠኝነት ያሳያል ያሉት ዶ/ር ተማም የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ቀጣይነት ባለው መልኩ የሞዴል ትምህርት ቤቱን በማስፋፋት ማህበረሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርግ እንዲሁም በትምህርት ጥራት ላይ ጉልህ ሚና የሚኖረው ስራ እንደሚሰራ አስታውቀዋል።


የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ/ም ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር የሚያስችለውን ዝግጅት በማጠናቀቅ ላይ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በተለይ የተማሪዎች እና መምህራን ምልመላ መስፈርት፣ የመማሪያ ክፍሎች እና የትምህርት ግብዓቶችን የማዘጋጀት ስራ እየተሰራ መሆኑ ተጠቁሟል።
Подробнее
]]>
https://linkbaza.com/catalog/-1001353914659 Mon, 11 Aug 2025 17:48:47 +0300
Подробнее
]]>
https://linkbaza.com/catalog/-1001353914659 Mon, 11 Aug 2025 17:48:22 +0300
Подробнее
]]>
https://linkbaza.com/catalog/-1001353914659 Sat, 09 Aug 2025 14:38:09 +0300
ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራን እና አመራሮች ልዩ አቅም ማጎልበቻ ስልጠና እየተሰጠ ነው
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
በድሬደዋ ዩኒቨርስቲ ካለፈው ሀምሌ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ከድሬደዋ አስተዳደር እና ከሶማሌ ክልል የተወጣጡ 336 የሁለተኛ ደረጃ መምህራን እና የትምህርት አመራሮች ልዩ የክረምት የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና እየተሰጣቸው ይገኛል፡፡

በዩኒቨርስቲው የመምህራን ልማትና ተከታታይ የሙያ ማሻሸያ ኦፊሰር የሆኑት መምህር ምንተስኖት ቦጋለ ስልጠናውን አስመልክቶ እንደተናገሩት በአገራችን ለትምህርት ጥራት መጓደል ከሚነሱት ምክንያት መካከል የመምህራን እና የትምህርት አመራሩ ብቃት ከሚፈለገው ደረጃ ላይ አለመገኘቱ ስልጠናውን መስጠት አስፈልጓል ብለዋል፡፡

የዚህ ልዩ የክረምት የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ዋነኛ አላማ የመምህራን እና የትምህርት አመራሩን የሙያ ብቃትና ተወዳዳሪነት በማሰደግ የተማሪዎች ውጤት እንዲሻሻል በማድረግ ሀገርን እና ወገንን የሚጠቅሙ ዜጎችን ማፍራት መሆኑን የሚያ ማሻሻያ ሶፊሰሩ ተናግረዋ፡፡

ስልጠናው የተለያዩ የትምህርት አይነቶች ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሰጥ ሲሆን ለማህበራዊ ሳይንስ መምህራን ለከታታይ 20 ቀን እንዲሁም ለተፈጥ ሳይንስ መምህራን ለተከታታይ 26 ቀን የሚሰጥ መሆኑ ከወጣው መርሃ ግብር ለመረዳት ተችልዋል፡፡

የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ሰልጣኞች በዩኒቨርሲቲው በሚኖራቸው ቆይታ አስፈላጊው የትምህርት ቁሳቁስ፣ የማደሪያ ቦታ፣ ምግብ አገልግሎት እና የቤተ ሙከራ ግብዓቶችን በማሟላት ሰልጣኞችን እያስተናገደ መሆኑ ተጠቁሟል።
Подробнее
]]>
https://linkbaza.com/catalog/-1001353914659 Thu, 07 Aug 2025 20:02:49 +0300
Подробнее
]]>
https://linkbaza.com/catalog/-1001353914659 Thu, 31 Jul 2025 13:48:05 +0300
Подробнее
]]>
https://linkbaza.com/catalog/-1001353914659 Wed, 30 Jul 2025 21:19:52 +0300
Подробнее
]]>
https://linkbaza.com/catalog/-1001353914659 Thu, 24 Jul 2025 21:14:15 +0300
Подробнее
10.83 k
]]>
https://linkbaza.com/catalog/-1001353914659 Thu, 24 Jul 2025 21:14:10 +0300
Подробнее
]]>
https://linkbaza.com/catalog/-1001353914659 Thu, 24 Jul 2025 20:55:42 +0300
Подробнее
]]>
https://linkbaza.com/catalog/-1001353914659 Thu, 24 Jul 2025 18:51:25 +0300
የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ከድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችል ስምምነት አደረገ።
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ተቋማትን የሚያዘምኑ ቴክኖሎጂዎችን በማበልፀግ እና ድጋፍ በማድረግ በርካታ ስራ እየሰራ ሲሆን የአስተዳደሩን ትምህርት ቢሮንም በተለይ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተናዎችን የሚያርም ሲስተም አበልፅጎ ማስተላለፉ ይታወሳል። መሰል ተቋማዊ የትብብር ስራዎችን መስራት የሚያስችል ስምምነት ደግሞ ዛሬ በሁለቱ ተቋማት ተፈርሟል።

የመግባቢያ ስምምነቱን የፈረሙት የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ኡባህ አደም እንደተናገሩት ‘’የትምህርት ጥራት እንደሀገር ትልቅ ትኩረት ተሰቶት እየተሰራ ሲሆን የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲም በተለይ ከትምህርት ዘርፉን በቴክኖሎጂ የማዘመን፣ የመምህራን እና ተማሪዎች ስልጠና እንዲሁም ትምህርት ቤቶችን የማደስ እና የማጣቀሻ መፅሃፍትን በማበርከት ሰፊ ስራዎችን እየሰራ ቆይቷል’’ ብለዋል።

የትምህርት ዘርፉን ስብራት ለማከም የሁሉንም ተቋማት እና የዘርፉን ምሁራን ርብርብ ይፈልጋል ያሉት ዶ/ር ኡባህ አደም የትምህርት ጥራንትን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራትን በመለየት፣ በማቀድ እና ተከታታይ ድጋፍ እና ክትትል በማድረግ ሊሰራ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሃላፊ አቶ ሱልጣን አሊዪ በበኩላቸው የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ አሰራሮችን የሚያዘምኑ ቴክኖሎጂዎችን ለትምህርት ቢሮ ማበርከቱን በማስታወስ ዩኒቨርሲቲው እገዛ ምስጋና አቅርበዋል። የትምህርት ቢሮ ሃላፊው በማከልም በሁለቱ ተቋማት መሀል የተደረገው ስምምነት ከዚህ በፊት የነበረውን ትብብር ከማጠናከሩም በላይ አስተዳደሩ ከትምህርት ጥራት ጋር ተያይዞ ለሚሰራቸው በርካታ ስራዎች እገዛ የሚያደርግ መሆኑን ጠቁመዋል።
Подробнее
]]>
https://linkbaza.com/catalog/-1001353914659 Thu, 24 Jul 2025 18:26:40 +0300
የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ እና ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በሀገር በቀል ዕውቀቶች ዙሪያ በትብብር ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ
👇👇👇👇👇👇👇
የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ እና የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በምስራቁ የሀገራችን ክፍል ያሉ የሀገር በቀል ዕውቀቶችን ዙሪያ በትብብር ምርምር ለመስራት፣ ካሪኩለም ለመቅረጽ፣ አወደ ጥናቶችን በትብብር ለማዘጋጀት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር ስራዎች ላይ በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።

በስምምነት ስነ-ስርዓቱ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ምርምር እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ተማም አወል እንደተናገሩት ‘’ ሀገር በቀል እውቀት የአንድ አካባቢ ማህበረሰብ ከአካባቢያዊ ሁኔታ ጋር ባለው ቁርኝት የሚገኝ እና የሚዳብር እንዲሁም ራሱን ከተፈጥሮ ጋር አስማምቶ ለማኖር የሚያስችል በዘመናት ሂደት የተገኘ እውቀት መሆኑን በመግልጽ ምስራቁ የሀገራችን ክፍል በሀገር በቀል ዕውቀቶች የበለፀገ እና ለሀገር ዘርፈ ብዙ አብርክቶት ያለው መሆኑን ጠቅሰዋል። ዶ/ር ተማም አክለውም ሁለቱ ዩኒቨርስቲዎች በሀገር በቀል እውቀቶች ላይ የሚያደርጉት ትብብር የማህበረሰቡ ውድ እቅቀቶች እና ክህሎት ተጠብቆ እንዲቆይ የሚያግዝ መሆኑን ተናግረዋል።

በተጨማሪም፣ የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና የማህበረሰብ ጉድኝት ም/ል ፕሬዚዳንት ዶ/ር ይስሐቅ የሱፍ ‘’ዛሬ የተፈራረምነው የመግባቢያ ሰነድ በምስራቁ የሀገራችን ክፍል ብሎም እንደ ሀገር ዘርፈ ብዙ ስራዎችን ለማከናወን የሚረዳና አባቶች ያቆዩልንን እነኝህን እውቀቶች ለአካባቢውና ለሀገር በሚጠቅም መንገድ በቴክኖሎጂ ሽግግርና በዲጂታል መንገድ በመስነድና ምርምር ስራዎች ላይ ትኩረት አድርገን መስራት የሚያስችል’’ ነው ብለዋል።
Подробнее
]]>
https://linkbaza.com/catalog/-1001353914659 Tue, 22 Jul 2025 21:27:39 +0300
ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የፋሲለደስ ስምምነት አካል የሚያደርገውን ስምምነት ከሰላም ሚኒስቴር ጋር ተፈራረመ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከሰላም ሚኒስቴር ጋር በመተባበር “ማህበራዊ ትስስራችን ለአብሮነታችን” በሚል መሪ ቃል የጎንደር የቃል ኪዳን ቤተሰብ ትስስርና ትውውቅ ሀገር አቀፍ የልምድ ልውውጥ አካሂዷል፡፡

በዚህ መርሀ-ግብር የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከተለያዩ ቦታዎች የሚመጡ ተማሪዎችን ‘’የቃል ኪዳን ቤተሰብ’’ በማድረግ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ትምህርት ብቻ ሳይሆን ከአካባቢው ማህበረሰብ እና የጎንደር ከተማ ነዋሪ ጋር ቤተሰብ የሚሆኑበትን እድል በማመቻቸት ሰፊ ስራ ሲሰራ ቆይቷል። ይህንኑ ተመኩሮ በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎችም ተግባራዊ እንዲሆን የሚያስችል ስምምነት በማስፈለጉ ዩኒቨርሲቲዎች እና ከተማ መስተዳደሮች እንዲሁም የሰላም ሚኒስተር ስምምነት አድርገዋል። ስምምነቱ የ ፋሲለደስ ስምምነት (Fasiledes Declaration) የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲሆን የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲም የስምምነቱ አካል መሆን ችሏል።

በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በኩል ስምምነቱን የፈፀሙት የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር እና ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሰለሞን ዘሪሁን እንደተናገሩት ‘’የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ መልካም ተሞክሮዎችን ከሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች በመቀመር የሚሰራ መሆኑ ገልፀው ተማሪን ከማህበረሰቡ ጋር ማቀራረብ እንዲሁም ቤተሰባዊ ትስስር መፍጠር ለተማሪውም ሆነ ዩኒቨርሲቲው ለሚገኝበት አካባቢ ማህበረሰብ በርካት ጠቀሜታ ይኖረዋል በለዋል።

ድሬደዋ፣ ሐምሌ 15፣ 2017 (የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ህዝብ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት)
Подробнее
]]>