#Orthodox_Tewahdo_new
Ethiopian Orthodox Tewahdo Church is a channel that broadcasts current news and teachings to the Christian public.
📢ለማስታወቂያ ሥራዎች 👉 @mane_tekel27
Информация о канале обновлена 21.11.2025.
#Orthodox_Tewahdo_new
Ethiopian Orthodox Tewahdo Church is a channel that broadcasts current news and teachings to the Christian public.
📢ለማስታወቂያ ሥራዎች 👉 @mane_tekel27
☦️የሕሊና ዳኛ☦️
❝ እግዚአብሔር በእያንዳንዳችን ሕሊና ውስጥ ኹል ጊዜ ንቁና ትጉ የኾነ ዳኛ ያስቀመጠው ስለምንድነው ? ብለህ ብትጠይቀኝ ፦ "ከሰው ወገን ይህን የሕሊና ዳኛን የመሰለ እንቅልፍ የለሽ ዳኛ ስለሌለ ነው፡፡" ብዬ እመልስልሃለኹ፡፡ ዳግመኛ የውጭ ዳኞች በገንዘብ ፣ በውሸት በመደለል ፤ የሐሰት ፍርድ እንዲሰጡ በማስፈራራት እንዲሁም በሌሎች መጠነ ብዙ ምክንያቶች ርቱዕ የኾነ ያልተዛባ ውሳኔአቸውን ሊያጣምሙ ይችላሉ፡፡
ጉቦ ብንሰጠው ፣ ልንዋሸው ብንሞክር ፣ ብናስፈራራው ፣ ሌላ ሌላም ብናደርግ እንኳን ይህ የሕሊና ዳኛ ለምናስበውና ለምንሠራው ኃጢአት ምንም ሳይጠመዘዝ እውነተኛ ፍርድን ይሰጣል፡፡
ኃጢአት የሠራ ሰው ሌላ ሰው ባይወቅሰው እንኳ እርሱ ራሱ ራሱን ይወቅሳል፡፡ አንዴ ወይም ኹለቴ ብቻ አይደለም ፤ መላ ዘመኑን እየደጋገመ ሕሊናው ይወቅሰዋል፡፡ ኃጢአት የሰራነው ከረጅም ዘመናት በፊት ሊኾን ይችላል፡፡ የሕሊናችን ዳኛ ግን ያን የሠራነውን ጥፋት ፈጽሞ አይረሳውም፡፡
የሕሊና ዳኛ ኃጢአት ከመስራታችን በፊትም ይኹን በኋላ ምንም ሳይሸፋፍን በግልጽ ይወቅሰናል ፤ በተለይ ደግሞ ከሠራነው በኋላ፡፡ ኃጢአት በምንሰራበት ሰዓት ግን ይህን ዳኛ አጥርተን አንሰማውም፡፡ ይኸውም በምንሰራው ክፉ ስራ ስለምንሰክር ነው፡፡ ኃጢአት መሥራታችንን ባቆምን ጊዜ ግን ወዲያው የጸጸት ሽመሉን ይመጀልጣል፡፡
ይህም በቀጥታ ምጥ ከያዛት ሴት ጋር ተቃራኒ ነው፡፡ እርጉዝ ሴት ምጥ የያዛት ጊዜ እጅግ አስጨናቂ የኾነ ሕመም ይሰማታል፡፡ ከወለደች በኋላ ግን በቃላት ሊገለጽ የማይችል ዕረፍት ይሰማታል፡፡ በወለደችው ልጅ ሐሴት ታደርጋለች፡፡ ኃጢአት ስንሠራ ግን ከዚሁ ተቃራኒ ነው፡፡ በሐሳብ የፀነስነውን ኃጢአት በግብር እስክንወልደው ድረስ "ደስታ" ይሰማናል፡፡ ክፉው ልጃችንን ኃጢአታችንን በግብር ከወለድነው በኋላ ግን በልጃችን ፊት ከፍተኛ ሐፍረት ይሰማናል፡፡ ምጥ ከያዛት ሴት በላይም ያሰቃየናል፡፡
ስለዚህ ልጆቼ ! ይህን ክፉ መሻት ከመጀመርያ አንስተን ከመቀበል እንከልከል፡፡ ከተቀበልነው እንኳ ገና ፍሬ ሳያፈራ ሳለ ከውስጣችን በገቢር ሳንገልጠው እንግደለው፡፡ ይህን ማድረግ ሳንችል ቀርተን ልጃችንን በገቢር በተግባር ከወለድነው ግን በንስሐና በዕንባ ለካህናት አባቶች በመናዘዝ ራሳችንንም በመውቀስ እንግደለው፡፡ † ❞
😇😇😇
😇😇😇ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ☦️
😇😇😇
😇"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"
📖ምሳ 1፥33
🤍ለወዳጆ ሼር ያድርጉ⚡️
╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ✧══╮
@Orthodox_Tewahdo_new
╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧• ✧══╯
#pray🙏#
ከዐሠርቱ ትእዛዛት ውስጥ የሚገርመኝ እውነታ ሁሉም ትእዛዝ የተነገሩት በነጠላ ለአንድ ሰው መሆኑ ነው፡፡ 'አድርግ አድርግ አታድርግ አታድርግ ሙሴ ዓሠርቱን ትእዛዛት ይዞ የወረደው በመቶ ሺህዎች ለሚቆጠሩት ለእስራኤላውያን ቢሆንም ትእዛዛቱ ግን አታምልኩ ፣ አትስረቁ ፣ በሐሰት አትማሉ ወዘተ የሚልአልነበረም፡፡ዐሥሩም በነጠላ አድርግና አታድርግ በሚሉ ትእዛዝና ሕግ የተሞሉ ናቸው፡፡ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ያለው ሃሳብ እንዲህ ነው፡፡ መስረቅ ሲያምርህ 'ሀገሩ ሁሉ እየሰረቀ ነው እኔ ብቻዬን ምን ለውጥ አመጣለሁ? ጊዜው የሌብነት ነው!' ብለህ አትጽናና፡፡ እግዚአብሔር 'አትስረቅ‛ እንጂ አትስረቁ አላለም፡፡ ሀገሩ ሁሉ ይስረቅ አንተ ግን 'አትስረቅ' የታዘዝከው ለብቻህ ነው ፤ የሚጠይቅህም ለብቻህ ነው፡፡
ማመንዘር በእኔ አልተጀመረ የማያመነዝር ማን አለ? ብለህ ለኃጢአትህ ማኅበርተኞች አታፈላልግ፡፡ 'አታመንዝር' ያለው ለአንተ ለብቻህ ነው፡፡ በባልንጀራህ ላይ በሐሰት አትመስክር ያለውም ላንተ ነው፡፡ 'የሥራው ጸባይ ነው፡፡ ሥራዬ መዋሸት ይጠይቃል' ብለህ ሐሰትህን የኑሮ መግፊያ ስልት አታድርገው፡፡
ብዙዎች በሐሰት ቢመሰክሩ አንተ ግን አትመስክር፡፡ ሁሉም መስክሮ እኔ ብቀር ምን ለውጥ ያመጣል? ብለህ ተስፋ አትቁረጥ። 'ብዙ ናቸው ብለህ ከክፉዎች ጋር አትተባበር' ፈጣሪህ ያዘዘህ ለብቻህ ነው፡፡ትዛዙን ከማይጠብቁ ከሺህ ሰዎች ይልቅ የእግዚአብሔርን ፍቃድ የሚያደርግ አንድ ይበልጣል (ሲራ 16:3)
😇"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"
📖ምሳ 1፥33
🤍ለወዳጆ ሼር ያድርጉ⚡️
╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ✧══╮
@Orthodox_Tewahdo_new
╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧• ✧══╯
#pray🙏#
#ዕለት:-ረቡዕ
#ቀን:- ኅዳር ፲ ፳፻፲፰ ዓ.ም☦️☦️
☦️☦️
☦️strongong>g>>☦️በዚችም ዕለት በእስክንድርያ አገር ሊቀ ጳጳሳት በድሜጥሮስ ዘመን ስለ ጾም ሥርዓት ቅዱሳን ሊቃነ ጳጳሳትና የኤጲስቆጶሳት የአንድነት ስብሰባ ተደረገ።
በዚህም የአንድነት ጉባኤ የመሰብሰባቸው ምክንያት እንዲህ ነው የክርስቲያን ወገኖች በጥር ዐሥራ አንድ ቀን በከበረች በጥምቀት በዓል ተጠምቀው በማግሥቱ የከበረች የአርባ ቀንን ጾም መጾም ይጀምራሉ እስከ የካቲት ሃያ ሁለት ቀንም ጾመው ጾምን ይፈታሉ።
ከዚህም በኋላ በመጋቢት በሃያ ሦስት የሕማማትን ሰሞን መጾም ይጀምራሉ በዚህም ወር በሀያ ሰባት የስቅለቱን በዓል ያከብራሉ በሃያ ዘጠኝም ክብር ይግባውና የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን የትንሣኤውን በዓል ያክብሩ ነበር።
ይህ ድሜጥሮስም በእስክንድርያ አገር ሊቀ ጳጳሳት ሁኖ በተሾመ ጊዜ በእርሻ የሚተዳደር መጻሕፍትን የማያውቅ ጨዋ ሰው ሲሆን እግዚአብሔር በመለኮታዊ ስጦታው ልቡን ብሩህ አድርጎለት የብሉይንና የሐዲስ መጻሕፍትን የቤተ ክርስቲያንንም ሕግ አወቀ ከእርሳቸውም ብዙዎችን ተረጎመ።
ከዚህም በኋላ በመንፈስ ቅዱስ ገላጭነት ባሕረ ሐሳብ የተባለ የዘመን ቁጥርን ጻፈ ይህም ክብር ይግባውና የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አጽዋማትና በዓላቶቹ የሚታወቁበት እሊህም የከበረች የአርባ ቀን ጾም የሆሣዕና ዑደት ስቅለቱ ትንሣኤው በአርባ ቀን ዕርገቱ ከትንሣኤውም በኋላ በኀምሳኛው ቀን መንፈስ ቅዱስ የወረደበት ናቸው።
ይህንንም ጽፎ ወደ ሮሜ አገር ሊቀ ጳጳሳት አባ ፊቅጦርላከ ሁለተኛም ወደ አንጾኪያ አገር ሊቀ ጳጳሳት አባ መክሲሞስ ላከ ዳግመኛም ወደ ኢየሩሳሌም አገር ሊቀ ጳጳሳት አባ አጋብዮስ ላከ እነርሱም በአነበቧት ጊዜ እጅግ ደስ ተሰኙባት።
የሮሜ አገር ሊቀ ጳጳሳት አባ ፊቅጦርም በሮሜ አገሮች ሁሉ ያሉትን ኤጲስቆጶሳቶቹን አዋቂዎችን ብዙዎች ሊቃውንትንም ሰበሰባቸው ይህንንም የዘመን ቁጥርአስነበበላቸው እጅግ በጣም ጥሩ ሁኖ አግኝተውት ደስ ተሸኙበት በደስታም ተቀበሉት አባዝተውም በመጻፍ ለሁሉ
አገሮች ላኩት እስከዚች ዕለትም ጸንቶ ተሠርቶ ኖረ።
ከዚህም በኋላ ልዩ ሦስት የሆነ አንድ እግዚአብሔርን ፈጽሞ እያመሰገኑት ወደየሀገራቸው ገቡ ለእርሱም ክብርምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን።🤲
ምንጭ፦📖መጽሐፈ ስንክሳር☦️
😇"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"
📖ምሳ 1፥33
🤍ለወዳጆ ሼር ያድርጉ⚡️
╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ✧══╮
@Orthodox_Tewahdo_new
╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧• ✧══╯
#pray🙏#share🔵
📕ጠቃሚ ምክር📕
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ "ለደካሞች ትጉላቸው" ብሎ በተናገረው መሠረት ምንጊዜም የሰዎችን ሞራልና መንፈስ ለመጠበቅ እንሞክር።
የሐዋርያውን ቃል በንቃት አድምጡ።
ለደካሞች ትጉላቸው ሰውን ሁሉ ታገሱ ።፩ኛ ቆሮ ፭ ÷ ፲፬ ሥሩን የሰደደ ኃጢያትን ነቅሎ ለመጣል ጊዜና ትዕግስት ስለሚጠይቅ እግዚአብሔር እንደነዚህ ያሉትን ደካሞች በጸጋው እስኪጎበኛቸውና ነጻ እስኪያወጣቸው ድረስ ትዕግሥት አድርጉላቸው።
አንተም ተፈጥሮህ ከእነርሱ ጋር ተመሳሳይ ስለሆነ ከዚህ የሚከተለውን የሐዋርያውን ቃል ዘወትር ከፊትህ አስቀድም።ከእነርሱ ጋር እንደ ታሰረ ሆናችሁ እስሮችን አስቡ የተጨነቁትን ደግሞ ራሳችሁ ደግሞ በሥጋ እንዳለ ሆናችሁ አስቡ ። ዕብ. ፲፪ ÷ ፫☦️ቅዱስነታቸው አቡነ ሽኖዳ☦️
🤍ለወዳጆ ሼር ያድርጉ⚡️
╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ✧══╮
@Orthodox_Tewahdo_new
╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧• ✧══╯
#pray🙏#share🔵ong>trong>
✨ሰብህዎ ለአምላክነ✨
ሰብህዎ ለአምላክነ ሃሌ ሉያ ለእግዚአብሔር /2/
በሰማይ በምድር/6/
አዝሰማዩን ያለምሰሶ አጽንቷል በቃሉ
መሬትን በውሆች መሃል መስርቷል በጥበቡ
ይታያል ያበራል ጌታ ዛሬም በስራው
ምስጉን ነው ሰራዊት ሁሉ ያመሰገነው
አዝምህረቱ ይቅርታው ብዙ ከወሰን የሰፋ
አባት ነው ብርቱ መጠጊያ የሰው ልጆች ተስፋ
መጋቢ ለፍጥረት ዓለም ታላቅ ባለጸጋ
ያብባል ይለመልማል እርሱን የተጠጋ
አዝተመስገን ተመስገን ይላል የተጎበኘ ሰው
ከጥፋት ከጉስቁልና ከሞት የመለሰው
ይቀባል ከታች አንስቶ ከእረኝነት ቦታ
ይቅርታው ጸጋው ብዙነው ምህረቱ የጌታ
አዝመላእክት በላይ በሰማይ ይዘምሩለታል
ዳዊትም ከበገናው ጋር በቅኔ ተነስቷል
በምድርም እኛ ልጆቹ እንበል ንሴብሆ
ይገባል ለአምላከ እስራኤል ውዳሴ አምልኮ
መዝሙር
☦️በመልዐከ ፀሐይ መኮንን ፍስሐ
🤍ለወዳጆ ሼር ያድርጉ⚡️
╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ✧══╮
@Orthodox_Tewahdo_new
╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧• ✧══╯
#pray🙏#share🔵
Владелец канала не предоставил расширенную статистику, но Вы можете сделать ему запрос на ее получение.
Также Вы можете воспользоваться расширенным поиском и отфильтровать результаты по каналам, которые предоставили расширенную статистику.
Также Вы можете воспользоваться расширенным поиском и отфильтровать результаты по каналам, которые предоставили расширенную статистику.
Подтвердите, что вы не робот
Вы выполнили несколько запросов, и прежде чем продолжить, мы ходим убелиться в том, что они не автоматизированные.
Наш сайт использует cookie-файлы, чтобы сделать сервисы быстрее и удобнее.
Продолжая им пользоваться, вы принимаете условия
Пользовательского соглашения
и соглашаетесь со сбором cookie-файлов.
Подробности про обработку данных — в нашей
Политике обработки персональных данных.