#News_Tewahdo
Ethiopian Orthodox Tewahdo Church is a channel that broadcasts current news and teachings to the Christian public.
Информация о канале обновлена 03.09.2025.
#News_Tewahdo
Ethiopian Orthodox Tewahdo Church is a channel that broadcasts current news and teachings to the Christian public.
እንደ መከላከያ መፍትሔ ይሆንህ ዘንድ ዘወትር ራስህን በሥራ ባተሌ አድርግ።
ዲያብሎስ ወደ እርሱ ገብቶ የወደደውን ዘር እንዳይዘራበት ሕሊናህን ባዶ አታድርገው።
መንፈሳዊ ንባብ ሕሊናን በሥራ ለመጥመድና መጥፎ አሳቦችን ለማራቅ ብቻ ሳይሆን ሌላም ታላቅ ጥቅም አለው። ንባብ ሕሊናን በተመስጦ ሊሞላ የሚችል መንፈሳዊ ዘዴ ከመስጠቱም በላይ ተቃዋሚ አሳቦችን የሚያጠፋውንና እግዚአብሔርን መውደድ የሚያስችለውን ስሜት በልብ ውስጥ ያጎናጽፋል።
📖ብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ📖
ሼር በማድረግ ለወዳጆ ያጋሩ‼️
⤴️ሼር // 𝐒𝐇𝐀𝐑𝐄
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@News_Tewahdo
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯
🛑የይቱብ ቻናላችን🛑
👇👇
🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘🔺
https://youtu.be/8tUjf9miCtQ?si=HGmQcv4jbX2F2IGI
፩. መዝሙረ ዳዊት
መዝሙረ ዳዊት በገዳማት ከሚኖሩ አበው መነኮሳት ባህታውያን ጀምሮ በካህናት፣ምእመናን በሁሉም ዘንድ በየእለቱ የሚጸለይ ጸሎት ነው ። አባቶች ከፊደል ቆጠራው ቀጥሎ ዳዊቱን ያጠኑና ከዚህ ጊዜ ጀምረው እየደገሙት፣እየጸለዩበት
ይኖራሉ።ዳዊት ሳይደግሙ ወደ
ዕለታዊ ተግባራቸው አይሰማሩም :: መዝሙረ ዳዊት እንደሌሎች ጸሎታት ሁሉ በየዕለቱ ተለይቶ የሚጸለይ አለው። ቀጥለን እንመልከት
ሰኞ ከ 1 - 30፣
ማክሰኞ ከ 31 – 60፣
ረቡዕ ከ 61 – 80፣
ሐሙስ ከ 81 –110፣
አርብ ከ 111 – 130፣
ቅዳሜ ከ 131 – 150
እሁድ- ጸሎተ ነቢያት እና መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን ይጸለያል ፡፡
አንድ ንጉሥ መዝሙረ ዳዊትን ስንጸልይ ለዕለቱ
የታዘዘውን ሃያ እና ሰላሳ መዝሙር ማድረስ ባንችል እንኳን አንድ ንጉሥ ማድረስ ይገባናል። አንድ #ንጉሥ የሚባለው ፦ #አስር_መዝሙር_ነው፡፡ለምሳሌ ሰከኞ አንድ ንጉስ ለማድረስ ከፈቀዱ ከ 1 – 10 ያለውን ያደርሳሉ፡፡ከማክሰኞ ከሆነ ደግሞ ከ 30 -40 ያውን የመጀመሪያውን አስር መዝሙር
ያደርሳሉ ማለት ነው፡፡ይህን ሁሉ ማድረስ ያልተቻለው ግን የተወሰኑ መዝሙራትን መርጦ በየእለቱ ያደርሳል፡፡
፪. ውዳሴ ማርያም
ውዳሴ ማርያም ከተቻለ የሰባቱን ዕለታት ካልተቻለ የእለቱን ማድረስ ተገቢ ነው ።የዘወትር ጸሎት ካደረስን በኋላ የዕለቱን ውዳሴ ማርያም አድርሰን ይዌድስዋ መላዕክትን ደግመን ከእመቤታችን በረከት ተሳታፊ መሆን ተገቢ ነው፡፡በዋልድባ የሚኖሩ መነኮሳት ውዳሴ ማርያም ከቅዳሴ ማርያም ሳያደርሱ ውለው አያድሩም፡፡
በየአብነት ትምህርት ቤቱ የሚገኙ መምህራንና ተማሪዎች እና በየገዳማት ያሉ መነኮሳት ሁሉ ውዳሴ ማርያምን በየዕለቱ ያደርሳሉ፡፡እኛም ከአበው ተምረን ማታ ከመኝታ በፊት ወይም ጠዋት ስንነሳ ይህን ጸሎት ማድረስ ተገቢ ነው፡፡
ይቀጥላል ..........
📖ትምህርቱን ለሌሎች እናካፍል !!!
ሼር በማድረግ ለወዳጆ ያጋሩ‼️
⤴️ሼር // 𝐒𝐇𝐀𝐑𝐄
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@News_Tewahdo
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯
🛑የይቱብ ቻናላችን🛑
👇👇
🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘🔺
https://youtu.be/8tUjf9miCtQ?si=HGmQcv4jbX2F2IGI
አምስተኛው የጸሎት ጊዜ የሠርክ ጸሎት ነው፡፡ስለዚህ የጸሎት ሰዓት ቅዱስ ዳዊት እንዲህ ይላል፡፡”ጸሎቴን እንደ ዕጣን በፊትህ ተቀበልልኝ እጅ መንሳቴም እንደ ሠርክ መሥዋዕት ትሁን” (መዝ 140 ÷2)
=> ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
ዓለምን ለማዳን በፈቃዱ ነፍሱን ከሥጋው ከለየ በኋላ ወደ መቃብር የወረደበት ሰዓት ነው፡፡
(ማቴ. 27÷ 57)
1.6 ጸሎተ ንዋም (የመኝታ ጊዜ ጸሎት)
ይህ ጊዜ ዕለቱን በሰላም አሳልፈን ለሌሊቱ ዕረፍት
የምንዘጋጅበት ነው ፡፡ በሰላም ላዋለን ፈጣሪ በሰላም አሳድረን ብለን ራሳችንን በእምነት የምናስረክብበት ነው፡፡እኛ ተኝተን የሚሆነውን አናውቅም እርሱ ግን የማያንቀላፋ እረኛ
ስለሆነ ይጠብቀናል።ስለዚህ ከመተኛታችን በፊት ሊሌሊቱን እንዲባርክልን እንጸልያለን።
በዚህ ጊዜ፡-
=> ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ
ዛሙርቱን በጌቴሴማኒ ጸሎት አስተምሯቸዋል፡፡
=> ቀኑ አልፎ በሌሊቱ ይተካል ስለዚህ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለጸሎት ማስተማሩን እያሰብን እንጸልያለን፡፡ሰላም አሳድረንም ብለን ለፈጣሪ ራሳችንን በእምነት አደራ እናስረክባለን፡፡
1.7 መንፈቀ ሌሊት (እኩለ ሌሊት)
·እኩለ ሌሊትም እንደ ቀናቱ የጸሎት ሰዓታት
የተለያዩ ትርጉሞች አሉት ። ቅዱሰ ዳዊት ‘’መንፈቀ ሌሊት እትነሣእ ከመ እግነይ ለከ በእንተ ኵነኔ ጽድቅከ”“ስለ ጽድቅህ ፍርድ በእኩለ ሌሊት
አመሰግነህ ዘንድ እነሳለሁ”/መዝ 118-62/በማለት ይህ ሰዓት ከእግዚአብሔር ጋራ የሚነጋገርበት እንደሆነ ገልጿል፡፡
=> ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቤተልሔም ዋሻ የተወለደበት ሰዓት ነው።
=> ሞትን ድል አድርጎ በታላቅ ኃይልም የተነሳው በሌሊት ነው።
=> ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግመኛ ለፍርድ ሚመጣበትም ሰዓት ነው። ከዚህ የተነሳ ለእኛ ሲል ከሰማየ ሰማያት
መውረዱን ፣ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ መወለዱን በማሰብ ሞትን ድል እንደነሳልንም
አስበን በማመስገን ዳግመኛ ለፍርድ ሲመጣ በቀኙ ከሚያቆማቸው ወገን እንዲያደርገን
እየለመንን በዚህ ሰዓት እንጸልያለን፡፡
✝ሰባቱን የጸሎት ጊዜያት ጠብቀን መጸለይ ካልተቻለንስ?
በሰባቱ የጸሎ ሰዓታት የታቻለንን ያህል እንድንጸልይ ታዘናል፡፡እነዚህን የጸሎት ሰዓታት በገዳም ያሉ መነኮሳት በየበረሃው የሚዞሩ ባሕታውያን ይጠብቋቸዋል፡፡ይጸልዩባቸዋልም ፡፡ በከተማ
በሥራ ምክንያት ሩጫ በዝቶበት በሁሉም ሰዓት መጸለይ የማይችል ክርስቲያን ግን ቢያንስ በማለዳ ከእንቅልፉ ሲነሳ እና ማታ ወደ መኝታው ሲያመራ መጸለይ ይገባዋል።ጠዋት እና ማታ በመጸለይ
ከፈጣሪ ጋራ ያለው የአባትና ልጅ ግንኙነት
እንዳይቋረጥ ማድረግ ይገባዋል፡፡
ይቀጥላል ..........
📖ትምህርቱን ለሌሎች እናካፍል !!!
ሼር በማድረግ ለወዳጆ ያጋሩ‼️
⤴️ሼር // 𝐒𝐇𝐀𝐑𝐄
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@News_Tewahdo
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯
🛑የይቱብ ቻናላችን🛑
👇👇
🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘🔺
https://youtu.be/8tUjf9miCtQ?si=HGmQcv4jbX2F2IGI
=>በዕፀ በለስ ምክንያት ለስሕተት የተዳረገውን አዳምን ለማዳን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቀራንዮ አደባባይ የዋለበት
=> የቀን እኩሌታ በመሆኑ የፀሐይ ሙቀት
የሚያይልበት የሰው ልጅ ለድካም የሚዳረግበት በዚህም ምክንያት አጋንንት የሚበረታቱበት ጊዜ ነው።
=> ስለዚህ የአዳምን ስሕተት፣ የዳግማዊ አዳም የኢየሱስ ክርስቶስ መሰቀልና መሞት፣እያሰብን የቀን እኩሌታ በመሆኑ መዳከማችንን ተገን
አድርጎ አጋንንት እንዳይሰለጥንብን እየለመንን እንጸልያለን፡፡
1.4 ተሰዓተ ሰዓት (9 ሰዓት)
ዘጠኝ ሰዓት ላይ አራተኛውን ጸሎት እናደርሳለን።በዚህ ጊዜ
=> ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
አዳምን ነጻ ለማውጣት በፈቃዱ ቅዱስ ሥጋውን ከቅድስት ነፍሱ የለየበት ሰዓት ነው።
=> ቅዱሳን መላእክት የሰው ልጆችን በጎም ሆነ
ክፉ ተግባር ወደ ፈጣሪ የሚያሳርጉበት ነው
=> ቆርኖሌዎስ የተባለ መቶ አለቃ በጸሎት ጸንቶ
ደጅ ሲጠና ከሰነበተ በኋላ ከፈጣሪው ምላሽ ያገኘበት ሰዓት ነው (ሐዋ 10÷ 9) በዚህ ጊዜ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መከራ እና ሞት አያሰብን ቅዱሳት መላእክት ከፈጣሪያቸው እንዲያስታርቁን እየለመንን የቆርኖሌዎስ እድል እንዲገጥመን እየተማጸንን እንጸልያለን ::
ይቀጥላል ..........
ትምህርቱን ለሌሎች እናካፍል !!!
ሼር በማድረግ ለወዳጆ ያጋሩ‼️
⤴️ሼር // 𝐒𝐇𝐀𝐑𝐄
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@News_Tewahdo
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯
🛑የይቱብ ቻናላችን🛑
👇👇
🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘🔺
https://youtu.be/8tUjf9miCtQ?si=HGmQcv4jbX2F2IGI
ነሐሴ ፳፬
በዚህችም ቀን ፦
● ☦️ጌታችን በቅዱስ አምላካዊ ቃሉ « ሐዲስ ሐዋርያ » ብሎ የሰየማቸው የኢትዮጵያ ብርሃኗ የሆኑ #አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት ዕረፍታቸው ነው ።
● ☦️ምግባር ሃይማኖት ፣ ገድል ትሩፋታቸው ከማር የጣፈጠ ሰማዕቱ #አቡነ_ቶማስ_ዘመርዓስ ዕረፍታቸው ነው ።
● ለ፲፪ ዓመታት በጉድጓድ ውስጥ በተጋድሎ የኖረች ፣ እንዲሁም በጣና ባሕር ውስጥ ገብታ ሰውነቷ ተበሳስቶ የባሕር ዓሣ መመላለሻ እስከሚሆን ድረስ እንደ ተተከለ ዓምድ ሆና ከባሕሩ ሳትወጣ 12 ዓመት ቆማ ስትጸልይ የኖረችው እናታችን #ቅድስት_ክርስቶስ_ሠምራ ዕረፍቷ ነው ።
● የአቡነ ዘርዐ ቡሩክ የአክስት ልጅ የሆኑት #አቡነ_ጊዮርጊስ_ዘግሽ ዕረፍታቸው ነው ።
+ አቡነ ፊልሞና ዘሽሬ ኢትዮጵያዊ
+ አቡነ ሰብሐት ለአብ ዘአኲሱም ኢትዮጵያዊ
+ አቡነ ቢንያም ዘጎንደር ኢትዮጵያዊ
+ አቡነ ዘሚካኤል ዘሞድ መታሰቢያቸው ነው።
መልካም በዓል
ሼር በማድረግ ለወዳጆ ያጋሩ‼️
⤴️ሼር // 𝐒𝐇𝐀𝐑𝐄
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@News_Tewahdo
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯
🛑የይቱብ ቻናላችን🛑
👇👇
🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘🔺
https://youtu.be/8tUjf9miCtQ?si=HGmQcv4jbX2F2IGI
📖የጸሎት ጊዜያት📖
ክፍል አንድ
ልበ አምላክ ነቢየ ልዑል ቅዱስ ዳዊት”ስብዓ
ለእለትየ እሴብሐከ በእንተ ኵነኔ ጽድቅከ ፣ስለ ጽድቅህ ፍርድ በቀን ሰባት ጊዜ አመሰግንሃለው”/መዝ 118-164/ብሎ እንደተናገረ ክርስቲያን የሆነ ሁሉ ሰባት ጊዜ በየእለቱ እንዲጸልይ ቤተ ክርስቲያን ታስተምረናለች ፡፡
ሰባቱ የጸሎት ጊዜያትም የሚከተሉት ናቸው::
1.1 ጸሎተ ነግህ
ቅዱስ ዳዊት “አምላኬ አምላኬ በማለዳ ወደ አንተ እገሰግሳለሁ” መዝ 62÷11 እንዳለ ሌሊቱ አልፎ ቀኑ ሲተካ ፣ ከመኝታችን ስንነሳ ምንጸልየው የጸሎት ዓይነት ጸሎተ ነግህ ይባላል፡፡ በዚህ ጊዜ የሚከተሉትን ምስጢራት እያሰብን መጸለይ ይገባናል፡፡
=> ሌሊቱን አሳልፎ ቀኑን ስለተካልን እያመሰገንን
ወጥተን እስክንገባ በሰላም ጠብቆ ውሎአችንን የተባረከ እንዲያደርግልን እንጸልያለን።
=> የመጀመሪያው ሰው አዳም የተፈጠረበትም
ሰዓት በመሆኑ ያንንእያሰብን እንጸልያለን፡፡
=> የሰውን ልጅ በመዓልትና በሌሊት የሚጠብቁ
መላእክት ለተልዕኮ ሲፋጠኑ የሚገናኙበት ሰዓት ነው፡፡የሌሊቱ መልአክ ሲሄድ የቀኑ መልአክ ሲቀርብና ሲተካ የሚገናኙበት በመሆኑ በዚህም ሰዓት እንጸልያለን፡፡
=>ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ
ሰው ልጆች በደል በጲላጦስ አደባባይ የቆመበት ሰዓት በመሆኑ እንጸልያለን።
1.2 ጸሎተ ሠለስት (3 ሰዓት)
ከነግህ በመቀጠል የምንጸልየው ጸሎት ጸሎተ ሠለስት (የሦስት ሰዓት) ጸሎት ይባላል ፡፡
ይህ የጸሎት ጊዜ
=> ሔዋን የተፈጠረችበት
=> እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የቅዱስ ገብርኤልን ብሥራት የሰማችበት
=> ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ
ሰው ልጆች ሲል በጲላጦስ አደባባይ የተገረፈበት
=> ነቢዩ ዳንኤል ፊቱን ወደ ኢየሩሳሌም አቅጣጫ መልሶ የቤቱን መስኮት ከፍቶ የጸለየበት
=> ለአባቶቻችን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ የወረደበት /በኢየሩሳሌም ጸንተው በመቆየታቸው ከእግዚአብሔር ዘንድ ይህንን ታላቅ ጸጋ የተቀበሉበት /ሰዓት ነው፡፡
ይቀጥላል ..........
ሼር በማድረግ ለወዳጆ ያጋሩ‼️
📱ሼር // 𝐒𝐇𝐀𝐑𝐄🌐
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@News_Tewahdo
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯
📺 የይቱብ ቻናላችን📺
👇👇
🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘🔺
https://youtu.be/yI-3Sl9NB5c
https://youtu.be/yI-3Sl9NB5c
"ማንስ ነው ከቅዱሳን ሁሉ በላይ እንደሆነች ያላስተዋለ? እግዚአብሔር ለአገልጋዮቹ የሚልቅ ጸጋን ከሰጠና የሚነኩት ሁሉ ከበሽታው ከተፈወሰ፣ ጥላቸው ያረፈበት ተአምር ከተፈፀመለት፣ ጴጥሮስ በጥላው ካዳነ (የሐዋ 5÷15)፣ የጳውሎስ የልብሱ ጨርቅ ዕራፊ መናፍስትን ካወጣ (የሐዋ 19÷11)፤ ለእናቱማ ምን አይነት ስልጣንና ኃይል ተሰጥቷት ይሆን?
ለቅዱሳኑ ይኽን ያኽል ድንቅ እንዲያደርጉ ባለሟልነትን ከሰጣቸው ወልዳ ላሳደገችው እናቱማ ምን ያኽል ይሰጣት ይሆን? በምን አይነት ስጦታ አስጊጧት ይሆን?
ጴጥሮስ "ክርስቶስ አንተ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ " ስላለው ብፁዕ ከተባለና የመንግስተ ሰማያት ቁልፍ ከተሰጠው (ማቴ16÷16-19)፤ እርሷ ከሁሉም ይልቅ እንዴት የተባረከች (ብፅዕት) አትሆን? (ሉቃ1÷45)፤
ጳውሎስ ታላቅ ክብር ያለውን የክርስቶስን ስም በመሸለሙ "ምርጥ እቃ" ከተባለ (የሐዋ 9÷15)፤ የአምላክ እናትማ የምእመናን ምግብ የኾነ መናውን ሳይሆን የሕይወት ሰማያዊ እንጀራን ያስገኘች እርሷ ምን አይነት ልዩ እቃው ትሆን?
ነገር ግን ስለ እርሷ ብዙ እናገራለሁ ብዬ ስለ ክብሯ ጥቂት በመናገር እራሴን በኅፍረት ውስጥ እንዳልጨምር እፈራለሁ ስለዚህ ካሁን ወዲህ የንግግሬን መልህቅ ስቤ በዝምታ ወደቤ ላይ ማረፍን መርጫለሁ"
☦️ቅዱስ ባስልዮስ☦️
ሼር በማድረግ ለወዳጆ ያጋሩ‼️
📱ሼር // 𝐒𝐇𝐀𝐑𝐄🌐
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@News_Tewahdo
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯
📺 የይቱብ ቻናላችን📺
👇👇
🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘🔺
https://youtu.be/yI-3Sl9NB5c
https://youtu.be/yI-3Sl9NB5c
📖"ነገር ኹሉ ለበጎ እንዲደረግ እናውቃለን!"📖
☦️አንዳንዴ በሕይወታችን ምንም የማይጠቅሙ ነገሮችን ልንመርጥ እንችላለን። የሚያስፈልገንና የማይጠቅመን ግን መንፈስ ቅዱስ ሲመርጥልን ነው።"
☦️አደጋና ስጋት፣ በሽታና ስቃይ፣ እጦትና ችግር፣ ረሀብና ጥማት፣ ኅዘንና ትካዜ፣ የሌለው ሕይወት እጅግ ጠቃሜ እንደ ኾነ አድርገን እናስባለን ነገር ግን ይህን የሌለው ሕይወት ኹሉ ጠቃሚ ላይኾን ይችላል።
☦️እንደ ራሳችን ሐሳብ ሳይኾን እንደ እግዚአብሔር ሐሳብ ስንጓዝ ግን ነገር ኹሉ ለበጎ ነው። ነገር ኹሉ ሲባልም በእኛ እይታ በጎ ነው የምንለው ብቻ አይደለም፡ ክፉ ነው የምንለውም ጭምር እንጂ። እንደ እግዚአብሔር ሐሳብ ሲሆን ማግኘትም፣ ማጣትም፣ ጤንነትም፣ በሽታም ለበጎ ነው።
☦️እግዚአብሔር ለእኛ መልካም የሚያደርግልን በጎ ነው ብለን በምናስበው ነገር ብቻ አይደለም። እጅግም ክፉና አስቸጋሪ መስለው ከሚታዩን ኹኔታዎችም ለእኛ ለልጆቹ እጅግ የሚደንቅ በጎ ነገርን ማድረግ ይችልበታል።
☦️ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ☦️
ሼር በማድረግ ለወዳጆ ያጋሩ‼️
📱ሼር // 𝐒𝐇𝐀𝐑𝐄🌐
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@News_Tewahdo
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯
📺 የይቱብ ቻናላችን📺
👇👇
🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘🔺
https://youtu.be/yI-3Sl9NB5c
https://youtu.be/yI-3Sl9NB5c
💡💡💡 ያጣ ለማኝ 💡💡💡
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
ቀበሮዋ አንድ የበሰለ የወይን ዛላ ተንጠልጥሎ ለመብላትም አስጎምጅቶ ታገኛለች፤ በመሆኑም በጣም ካልዘለለች በስተቀር እንደማታገኘው ስለታወቃት እንጣጥ እያለች ብዙ ሞከረች።
ይሁን እንጂ ወይኑ እንዳሰበችው በቀላሉ የምትደርስበት አልሆነም። ወደኋላ ተንደርድራ በጣም ዘለለችና የመጨረሻ ሙከራ አደረገች። ይሁን እንጂ ፈጽሞ ልትደርስበት አልቻለችም። ወይኑ በአለባበሱ በጣም ልዩ ነው፤ ለዐይን የሚያምር ለመብላትም የሚያስጎመጅ ነው። ወይኑን ትታ እንዳትሄድ ያስጎመጃል እንዳትበላው ደግሞ ስትዝል ብትውልም አልደረሰችበትም። ስለዚህ ''እንደውም ይኼ ወይን አልበሰለም'' ብላ ትታው ሔደች።
🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟🌟
"ያጣ ለማኝ ተሳድቦ ይሔዳል'' የሚባለው ለእንደዚህ ዐይነቱ ነው። የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለመናፍቃን ያልተመቸችው አላዋቂ ወገኖቻችን እንደሚሉት የዶግማና የቀኖና ችግር ኖሮባት ሳይሆን ይህንን መኖርና መፈጸም ስላቃታቸው ብቻ ነው።
መጾም ያቃታቸው ጾምን አያስፈልግም ሲሉ ንጽሕናቸውን ያጎደፉና ቆባቸውን የጣሉት ደግሞ ምንኩስና አያስፈልግም ይላሉ። ያቃተንንና ያልተደረሰበትን ነገር ሁሉ አያስፈልግም ብሎ መንቀፍ የቀበሮ ጠባይ ነው።
የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሥጋዊ ዕውቀት የማትመረመር ብትሆንም ትምህርቷ ግልጽ፤ ተልኮዋም የታወቀ ነው "ወንጌላችን የተከደነ ቢሆንም እንኳ የተከደነባቸው ለሚጠፉት ነው" እንዲል 1ኛቆሮ 4፥3
ሼር በማድረግ ለወዳጆ ያጋሩ‼️
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@News_Tewahdo
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯
📺 የይቱብ ቻናላችን📺
👇👇
🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘🔺
https://youtu.be/yI-3Sl9NB5c
https://youtu.be/yI-3Sl9NB5c
🟢ልጄሆይ ሳይረፍድብህ በፊት በራስህ ፍረድ፡፡
🟢ልጄ ሆይ በእግዚአብሔር ፊት ስትቆም ልክ የእሳት ፍም አጠገብ እንደ ቆምክ አስብ፡፡
🟢ልጄ ሆይ ከመንግሥተሰማይ እንዳትለይ ንስሐን ገንዘብ አድርጋት፡፡
🟢ልጄ ሆይ ሐጢአት ከሰው አይርቅም ሰው ግን ከሐጢአት ይርቃል፡፡
☦️ምክረ አበው☦️
ሼር በማድረግ ለወዳጆ ያጋሩ‼️
📱ሼር // 𝐒𝐇𝐀𝐑𝐄🌐
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@News_Tewahdo
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯
📺 የይቱብ ቻናላችን📺
👇👇
🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘🔺
https://youtu.be/8tUjf9miCtQ?si=HGmQcv4jbX2F2IGI
Владелец канала не предоставил расширенную статистику, но Вы можете сделать ему запрос на ее получение.
Также Вы можете воспользоваться расширенным поиском и отфильтровать результаты по каналам, которые предоставили расширенную статистику.
Также Вы можете воспользоваться расширенным поиском и отфильтровать результаты по каналам, которые предоставили расширенную статистику.
Подтвердите, что вы не робот
Вы выполнили несколько запросов, и прежде чем продолжить, мы ходим убелиться в том, что они не автоматизированные.