በዚህ ቻናል ዲ/ዮርዳኖስ የሚያስተምራቸው ወቅታዊ እና የነገረ ቅዱሳን (ዝክረ ቅዱሳን ትምህርቶችን ከእርሱ በመቀበል እናስተላልፋለን):: "ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
Информация о канале обновлена 06.10.2025.
በዚህ ቻናል ዲ/ዮርዳኖስ የሚያስተምራቸው ወቅታዊ እና የነገረ ቅዱሳን (ዝክረ ቅዱሳን ትምህርቶችን ከእርሱ በመቀበል እናስተላልፋለን):: "ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
✝ጾመ ጽጌን ለምትጾሙ ታላላቆቼ : እህቶቼና ወንድሞቼ . . .
❀እንኩዋን አደረሳችሁ!
❀በውስጥ መስመር ጥቂቶቻችሁ ጾሙ መቼ እንደሚገባ ጠይቃችሁኛል።
#ጾመ_ጽጌ ሁሌም ቢሆን የሚገባው መስከረም 26 ነውና ሊቀየር አይችልም።
❀ስለዚህ ከነገ (መስከረም 26) ጀምሮ ጾመ ጽጌ ትገባለች።
❀ላደለው፥ አቅሙም ላለው ይህንን ጾም መጾም ታላቅ ክብርና ፍቅር ነው።
❀የማንጾምም ብንሆን በሚቀጥሉት 40 ቀናት ተድላ ደስታ ባናበዛ ጥሩ ነው።
❀ጊዜው የፈጣሪ ስደትና የድንግልም መከራዋ የሚታሰብበት ነውና ማዘን ይገባል።
❀ነገር ግን በእነዚህ 40 ቀናት ሠርግን ጨምሮ ተድላ ሥጋን አብዝቶ መከወን ከአሳዳጁ ሔሮድስ ጋር መወገን ነውና እናስብበት።
❀በተለይ ሠርግ ማድረጉ ይከብዳል።
❀ግን ጾሙ የፈቃድ ነውና የሚጾመው በትህትናና በፍቅር ሊያደርገው ይገባል።
❀አድሏችሁ የምትጾሙ ወገኖቼም በጸሎታችሁ አስቡን❀
☞ሁላችንንም በድንግል ፍቅር ከልሎ ለዚሁ ማዕረግ ያብቃን:: አሜን::
https://t.me/zikirekdusn
ንትፈሳሕ እስመ ሠረቀ ዮም ወርኃ ጽጌ፤
ወከመ ንዘከር ሕማማ ለማርያም ወለተ ሐጌ፤
ወለወልዳ ከሃሊ ኀጢአተ ዓለም ኃዳጌ፤
መምህራን ይቤልዋ ዘሰሎሞን ሐርጌ፤
ወለንግደታ አምኃ ዘአልቦ ኑታጌ!
https://t.me/zikirekdusn
✞ St. Zacharias, because he was a human and argued from joy, was made dumb. But Saint Elisabeth conceived the great man on Meskerem 26 (October 06) and concealed herself for 6 months. On the six month, when the Lord of all creation was conceived (assumed flesh [human nature]), the Queen of Heaven, our Lady, the Virgin Mary came to Elisabeth through the hill country. Since, the two saints were daughters of sisters.
✞When the Theotokos (Mother of God) reached and saluted them, the Holy Spirit descended upon the mother and child; hence Elisabeth praised and John while in the womb leaped (prostrated) with joy. Then, he was born on Sene 30 (July 07) and Zacharias, his father, spoke while he named him “John.”
✞✞✞ May the supplication and intercession of our Lady and the mercy of her beloved Child be truly with us. And may He multiply the Baptist’s blessing up on us.
✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 26th of Meskerem
1. The Virgin St. Mary
2. St. Joseph the elder (the betrothed)
3. St. John the Baptist (His conception)
4. Sts. Zacharias and Elisabeth
5. St. Aboli (Apoli) the Martyr (Translation of his relics)
✞✞✞ Monthly Feasts
1. St. Thomas the Apostle
2. Abune Habte Maryam
3. Abune Iyesus Moa
4. Saints, Martyrs of Najran
5. Saint Abune Selama Kesate Birhan
✞✞✞ “when Elisabeth heard the salutation of Mary, the babe leaped in her womb; and Elisabeth was filled with the Holy Ghost: And she spake out with a loud voice, and said, Blessed art thou among women, and blessed is the fruit of thy womb. And whence is this to me, that the mother of my Lord should come to me? …And blessed is she that believed: for there shall be a performance of those things which were told her from the Lord.”✞✞✞
Luke 1:41-45
✞✞✞ Salutation to God ✞✞✞
(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)
🔗https://t.me/zikirekdusn
▶️https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
Feasts of Meskerem 26
✞✞✞On this day we commemorate the Miracle of the Virgin St. Mary and the feast of St. John the Baptist✞✞✞
✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞
✞✞✞The Miracle of St. Mary✞✞✞
=> A miracle is a great sign, a happening that’s supernatural and an act that can’t be done with human capabilities. A miracle, when done by our Lord is of His own nature. And when done by the saints is of grace. In Holy Scripture, miracles done by the beloved of God are numerous. But
*It should be understood that miracles can also originate from demons.
*One should not seek out miracles (signs) on a daily basis.
*Trying [from which source the signs originate] and discerning are expected from a Christian.
*As St. John Chrysostom told us in his homily, performing miracles does not save one from the fires of hell. The Lord had also elaborated on the matter (Matthew 7:22, 12:39).
✞There is none that has performed as many miracles after God our Lord as that of the Virgin Mary. Leaving the other signs, she has done many miracles in each of our lives, we, ourselves, are the witnesses. The miracles of our Lady started from the time of the creation of the world.
✞Of course, to comprehend this it takes a broad and grasping mind. The Virgin Mary is the treasury of the mercy of God, she is the entrance of His grace. This is because He chose and loved this. The Mother of Light, after her conception and birth, performed many mighty things. The miracle she did on this day, 2007 years ago, was marvelous.
✞Her uncle, guardian and servant, St. Joseph the elder, after he brought her from the temple, used to chop wood. The time was a period of hardship and he had went for work for months and returned from a far land.
✞He had a philosopher friend called John who told the elder Joseph what he had not noticed. He said, “This child has conceived, inquire into the matter” and went. St. Joseph was shocked. He said, “Let alone in act she doesn’t think of such things” and entered to the house.
✞Then he asked our Lady, “My child! From whom did you conceive?” She replied, “Of the [economy of the] Holy Spirit”. He was confused. The mystery was hidden from him. He started inquiring and worrying saying, “How could a woman conceive without the seed of man?” But, when she noticed that he was anxious, our Lady called him and took him outside.
✞She lodged in the ground a chopped wood that he had left a long time ago and prayed over it. Within a minute, while the elder was looking with his eyes, that dry wood sprouted, bloomed and bore fruit. He was extremely shocked.
✞She said, “My father look! Who did this?” He answered, “My daughter and my lady! It is God.” And she replied, “The one in my womb is God, about Whom Isaiah prophesized, Who is almighty.” And the elder, as St. Iraklis, in the ‘Faith of the Fathers’, told us by saying “bowed to her”, prostrated before her on the ground.
✞✞✞ St. John the Baptist ✞✞✞
=>It is difficult to say that, in the Gospel, there is someone whose honor was mentioned as much as the family of Zacharias, except our Lady. St. Luke started his Gospel with this family and the Holy Spirit inspired him to write the following. Says, “And they were both righteous before God, walking in all the commandments and ordinances of the Lord blameless.”(Luke 1.6)
✞ Let’s leave ‘before mankind’, but how transcendent is it to live blameless before God? And to this, awe is appropriate! These, holy husband and wife, were far gone in years without bearing a child as they were barren.
✞ According to the Tradition of the Church, the age of Elisabeth was 90 and Zacharias had reached 100. But the Lord who saw their patience, sent the angel of annunciation, St. Gabriel, to give them [annunciate the birth of] a great prophet, who was greater than men and about whom a prophecy was told about (Isaiah 40.3/ Malachi 3.1).
††† እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እና ለቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††
††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††
††† ተአምረ ማርያም †††
††† ተአምር ማለት "ድንቅ: ምልክት: ከተፈጥሮ ሥርዓት ውጪ የሆነ ክዋኔ: በሰብአዊ አቅም ሊሠራ የማይችል ተግባር (ድርጊት)" ነው:: ተአምራት ከባለቤቱ ከጌታችን ሲሆኑ የባሕርዩ ናቸው:: ከቅዱሳኑ ሲሆኑ ደግሞ የጸጋ እንላቸዋለን:: ቅዱስ መጽሐፍ ላይ በእግዚአብሔር ወዳጆች የተሠሩ ተአምራት እጅግ ብዙ ናቸው:: ነገር ግን:-
*ተአምራት ከአጋንንትም ሊሆኑ እንደሚችሉ መረዳት::
*ሁሌ ምልክትን (ተአምርን) አለመፈለግ::
*መመርመርና ማስተዋል ከአንድ ክርስቲያን ይጠበቃል::
*ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ በድርሳኑ እንደ ነገረን ተአምር መሥራት ከሲዖል እሳት አያድንም:: ጌታም በዚህ ነገር ተባብሮበታል:: (ማቴ. 7:22, 12:39)
ከጌታችን እግዚአብሔር ቀጥሎ የድንግል ማርያምን ያህል ተአምራትን የሠራ አይገኝም:: እንዲያው ሌላውን ትተን በእያንዳንዳችን ሕይወት ላይ እንኳ ብዙ ድንቅ ነገሮችን አድርጋለችና ምስክሮቹ እኛው ራሳችን ነን:: የእመቤታችን ተአምር የተጀመረው ገና ከፍጥረተ ዓለም ነው::
በእርግጥ ይህንን ለመረዳት ሠፊ አዕምሮና አስተዋይ ልቡናን ይጠይቃል:: ድንግል ማርያም ማለት የእግዚአብሔር የቸርነቱ ግምጃ ቤት: የጸጋው ደጅ ናት:: እርሱ ይህንን መርጦ ወዷልና:: እመ ብርሃን ተጸንሳ ከተወለደች በኋላ ደግሞ እጅግ ብዙ ኃይልን ታደርግ ነበር:: በዚህ ዕለት ከ2007 ዓመታት በፊት ያደረገችው ተአምር ደግሞ ድንቅ ነው::
አጐቷ /ጠባቂዋ/ አገልጋዩዋ አረጋዊ ቅዱስ ዮሴፍ ከቤተ መቅደስ ተቀብሎ ካመጣት በኋላ እርሱ እንጨትን ይጠርብ ነበር:: ዘመኑ ዘመነ ዐጸባ (የችግር ዘመን) በመሆኑ ለሥራ ጉዳይ ወደ ሩቅ ሃገር ሒዶ የተመለሰው ከወራት በኋላ ነው::
ዮሐንስ የሚሉት ፈላስፋ ባልንጀራ ነበረውና ሽማግሌው ዮሴፍ ልብ ያላለውን ነገር ነገረው:: "ይህች ብላቴና ጸንሳለችና መርምራት" ብሎ ሔደ:: ቅዱስ ዮሴፍ ግን ደነገጠ:: "እኔ እንዲህ ያለ ነገር እንኳን በገቢር (በሥራ) በሃሳብም አላውቅባት" ብሎት ወደ ቤት ገባ::
ቀጥሎም እመቤታችንን "ልጄ ሆይ! ከማን ጸነስሽ" አላት:: "እመንፈስ ቅዱስ" አለችው:: ግራ ገባው: ምሥጢርም ተሠወረበት:: "እንዴት አንዲት ሴት ያለ ወንድ ዘር ልትጸንስ ትችላለች?" ብሎ ያወጣ: ያወርድ: ይጨነቅም ገባ:: የእኛ እመቤት ግን እንደ ጨነቀው ባወቀች ጊዜ ጠርታ ወደ ውጪ ይዛው ወጣች::
ከረዥም ጊዜ በፊት ጠርቦ የጣለውን እንጨት አንስታ ተከለችውና ጸለየችበት:: በደቂቃም የአረጋዊው ዐይን እያየ ያ ደረቅ እንጨት ለምልሞ: አብቦ አፈራ:: ቅዱስ ዮሴፍ በጣም ደነገጠ::
"አባቴ ተመልከት እስኪ! ይህንን ማን አደረገ?" አለችው:: "ልጄና እመቤቴ! እግዚአብሔር ነው" አላት:: እርሷም "በማሕጸኔ ያለውም ኢሳይያስ ትንቢትን የተናገረለት አምላክ ነውና ሁሉን ይችላል" አለችው:: አረጋዊውም ቅዱስ ኤራቅሊስ በሃይማኖተ አበው እንደ ነገረን "ሰገደ ላቲ" ወደ ምድር ወድቆ በፊቷ ሰገደ::
††† ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ †††
††† ቅዱስ ወንጌል ላይ ከእመቤታችን ቀጥሎ የዘካርያስን ቤተሰብ ያህል ክብሩ የተገለጠለት ፍጡር ይኖራል ብሎ መናገሩ ይከብዳል:: ቅዱስ ሉቃስ የጀመረው በዚህ ቅዱስ ቤተሰብ ነውና መንፈስ ቅዱስ እንዲህ ሲል አጽፎታል:: "ዘካርያስ ካህኑና ቅድስት ኤልሳቤጥ በሰውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ የሚኖሩ ጻድቃን ነበሩ" ይላቸዋል:: (ሉቃ. 1:6)
የሰውን እንተወውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ መኖር ምን ይረቅ? ለዚህ አንክሮ (አድናቆት) ይገባል! እሊህ ቅዱሳን ባልና ሚስት ግን መካኖች በመሆናቸው ልጅ ሳይወልዱ ዘመናቸው አልፎ ነበር::
እንደ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት ዕድሜአቸው የኤልሳቤጥ 90 የዘካርያስ ደግሞ 100 ደርሶ ነበር:: ፍጹም መታገሳቸውን የተመለከተ ጌታ ግን በስተ እርጅናቸው ከሰው ሁሉ በላይ የሆነ: ትንቢት ለብቻው የተነገረለት (ኢሳ. 40:3, ሚል. 3:1) ታላቅ ነቢይን ይሰጣቸው ዘንድ መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤልን ላከላቸው::
ቅዱስ ዘካርያስ ሰው ነውና ከደስታ ብዛት በመከራከሩ ድዳ ሆነ:: ቅድስቲቷ ግን መስከረም 26 ቀን ታላቁን ሰው ጸንሳ ለ6 ወራት ራሷን ሠወረች:: በ6ኛው ወር የፍጥረት ሁሉ ጌታ በተጸነሰ ጊዜ የአርያም ንግሥት ድንግል እመቤታችን ደጋ ደጋውን ወደ ኤልሳቤጥ መጣች:: ሁለቱ ቅዱሳት የእህትማማች ልጆች ናቸው::
የአምላክ እናቱ ስትደርስና "ሰላም" ስትላቸው መንፈስ ቅዱስ በእናትና ልጅ ወርዶ ኤልሳቤጥ በምስጋና: ዮሐንስ ደግሞ ገና በማሕጸን ሳለ በደስታ ዘለለ (ሰገደ):: ከዚህ በኋላ ሰኔ 30 ተወልዶ: አባቱ ዘካርያስ "ዮሐንስ" ሲለው አንደበቱ ተፈትቶለታል::
††† የእመቤታችን ልመናዋ: ክብሯ: የልጇ የወዳጇም ቸርነት በእውነት ከሁላችን ጋር ይሁን:: የመጥምቁንም በረከት ያብዛልን::
††† መስከረም 26 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅድስት ድንግል ማርያም
2.ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ
3.ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ (ጽንሰቱ)
4.ቅዱሳን ዘካርያስና ኤልሳቤጥ
5.ቅዱስ አቦሊ ሰማዕት (ፍልሠቱ)
††† ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ቶማስ ሐዋርያ
2.አቡነ ሐብተ ማርያም ጻድቅ
3.አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ
4.ቅዱሳን ሰማዕታተ ናግራን
5.ቅዱስ አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን
††† "ኤልሳቤጥም የማርያምን ሰላምታ በሰማች ጊዜ ጽንሱ በማሕጸኗ ውስጥ ዘለለ:: በኤልሳቤጥም መንፈስ ቅዱስ ሞላባት:: በታላቅ ድምጽም ጮኻ እንዲህ አለች:-
'አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ: የማሕጸንሽም ፍሬ የተባረከ ነው:: የጌታየ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል? . . . ከጌታ የተነገረላት ቃል ይፈጸማልና ያመነች ብጽዕት ናት::" †††
(ሉቃ. ፩፥፵፩)
††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††
🔗https://t.me/zikirekdusn
▶️https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
"" የእስረኞች ጩኸት ወደፊትህ ይግባ ""
❖በምስል (Video) ለምትሹ፦
(መስከረም 23 - 2018)
https://youtu.be/AJjh5zQpvtU?si=yxnLMgBAIosUPwBY
ዘመነ ክረምት ቡሩክ ዮም ተፈጸመ፤
በሰላመ እግዚአብሔር መሐሪ ዘእንበለ ንርአይ ሕማመ፤
በእንተ ዝንቱ ነአኲቶ ለዘፈጠረ ዓለመ፤
በእንተ ማርያም ድንግል ዘረሰያ እመ፤
ከመ ያብጽሐነ በኂሩቱ ዓመ ከመ ዮም ዳግመ!
ዝክረ ቅዱሳን - (ርቱዓነ ሃይማኖት)
https://t.me/zikirekdusn
Владелец канала не предоставил расширенную статистику, но Вы можете сделать ему запрос на ее получение.
Также Вы можете воспользоваться расширенным поиском и отфильтровать результаты по каналам, которые предоставили расширенную статистику.
Также Вы можете воспользоваться расширенным поиском и отфильтровать результаты по каналам, которые предоставили расширенную статистику.
Подтвердите, что вы не робот
Вы выполнили несколько запросов, и прежде чем продолжить, мы ходим убелиться в том, что они не автоматизированные.