ፍልስፍና እውነትን በመፈለግ- ልማዳዊ እምነቶችን በመሞገት እና ጭፍን አመለካከቶችን በጥበብ በመመርመር ወደ ላቀ አሰተሳሰብ ያሻግራል።
በዚህ ቻናል አለም ላይ ያሉ ፍልስፍናዎች ፤ ርዕዮት አለሞች ፤ ሀይማኖቶች እና አስተሳሰቦች በነፃነት ይዳሰሳሉ።
Информация о канале обновлена 20.11.2025.
ፍልስፍና እውነትን በመፈለግ- ልማዳዊ እምነቶችን በመሞገት እና ጭፍን አመለካከቶችን በጥበብ በመመርመር ወደ ላቀ አሰተሳሰብ ያሻግራል።
በዚህ ቻናል አለም ላይ ያሉ ፍልስፍናዎች ፤ ርዕዮት አለሞች ፤ ሀይማኖቶች እና አስተሳሰቦች በነፃነት ይዳሰሳሉ።
እግዚአብሔር ስለምን ሰይጣንን አይምረውም!?
እግዚአብሔር ሰይጣንን ከማጥፋት ይልቅ ቢምረው ከባህሪው ጋር ይሄዳል።በመሆኑም ምህረት ባህሪው የሆነ አምላክ ሰይጣንንም ከማጥፋት ይልቅ ቢምረው ለሰው ልጅ ደህንነት እጅግ የላቀ አስተዋፅኦ ይኖረዋል፡፡ እውነት ግን እግዚአብሔር ስለምን ሰይጣንን አይምረውም!?
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ታሪክ ውስጥ እግዚአብሔር ለሰይጣን ምህረት እንዲያደርግ የተደረገ ሙከራ እንዳለ አውቃለሁ፡፡ ሙከራውም በቅድስት ክርስቶስ ሳምራ አማካኝነት የተደረገ ነው፡፡
ከዚህም በኋላ ክርስቶስ ሳምራ አቤቱ ፈጣሪ እኔን ባሪያህን ከክፉ ነገር ሁሉ ሰውረኸኛልና ዲያብሎስን ትምረው ዘንድ እለምንኻለሁ አለችው፡፡ ይኸውም ወድጄው አይደለም፤ ስለ አዳምና ስለ ልጆቹ በጠቅላላው ስለ ሰብዓ አለም ስጋቸው ስጋዬ ስለሆነ እንዳያስታቸው ክፉ ሥራ እንዳያሰራቸው ብዬ ነው ማርልኝ ማለቴ አለችው፡፡”
ሆኖም ግን ይህ የክርስቶስ ሳምራ ልመና በሰይጣን እምቢተኝነት ሊሳካ አልቻለም፡፡እንደ ጥንታዊት ግሪክ ፈላስፋ ሄራክላይተስ አመለካከት ግን ይሄ የቅድስት ክርስቶስ ሰምራ ልመና ከንቱ ነው፡፡ ምክንያቱ ደግሞ እግዚአብሔር ሰይጣንን ያልማረው ክርስቶስ ሳምራ እንዳለችው ሰይጣን እምቢተኛ ሆኖ ሳይሆን እግዚአብሔር ለሰይጣን ምህረትን ማድረግ ስለማይችል ነው፡፡ እንደ ሄራክላይተስ አመለካከት ዓለም ፍቅርና ጥላቻ፣ ጤናና በሽታ፣ ወንድና ሴት፣ ክረምትና በጋ፣ እኩይና ሰናይ፣ ሰይጣንና እግዚአብሔር በሚባሉ የቅራኔዎች ትግልና አንድነት ሕግ የሚመራ ነው፡፡
በዚህ የቅራኔዎች ትግልና አንድነት ሕግ መሰረት ደግሞ እግዚአብሔር ለሰይጣን ምህረት ማድረግ የማይችልበት ምክንያቶች አሉ፡፡
የመጀመሪያው ምክንያት በዚህ የቅራኔዎች ትግልና አንድነት ሕግ መሰረት አንደኛው የራሱን ትርጉምና ምንነት የሚያገኘው በተቃራኒው መኖር በመሆኑ ነው፡፡ ጨለማ ከሌለ ብርሃን ትርጉም አይኖረውም፤ በሽታ ከሌለ ጤና ምስጋናውን ያጣል፤ ኩነኔም ከሌላ ፅድቅ ምናምን ይሆናል፤ እንደዚሁም ሁሉ ሰይጣን ከሌለ እግዚአብሔርም ምንነቱንና አስፈላጊነቱን ያጣል፡፡
የሰው ልጅ እግዚአብሔርን በንፅፅር ካልሆነ ለብቻውና በምልዑነቱ መገንዘብ አይችልም፤ ማነፃፀሪያውም በተቃርኖ ውስጥ መገኘት አለበት፡፡ ምክንያቱም የአንድን ነገር ክስተት ወይም ስሜት፣ ምንነትና ባህሪ የምናውቀው ከተቃራኒው ምንነትና ባህሪ ጋር በማነፃፀር ስለሆነ፡፡ በዚህም መሰረት ስለ እግዚአብሔር ለማወቅ የግድ ሰይጣን መኖር አለበት፡፡ በቅራኔዎች ትግልና አንድነት ህገ መሰረት የሰይጣን ባህሪ ከእግዚአብሔር አንፃር የእግዚአብሔርም ባህሪ ከሰይጣን አንፃር ይታወቃል፡፡ ይላል
በርካታ ሃይማኖቶች ሰይጣንን በማውገዝ ላይ የተመሰረተ እምነት ቢኖራቸውም የሰይጣን መኖር ግን ለራሳቸው ለሃይማኖቶቹ ህልውና ሳይቀር አስፈላጊ መሆኑን አይገነዘቡም፡፡ ገጣሚና ፈላስፋው ካህሊል ጅብራንም “Satan” በሚለው አጭር መጣጥፉ ውስጥም የሚለው ይሄንኑ ነው፤
“የሠይጣን መኖር ሃይማኖትንና ቤ/ክንን ከማቋቋሙም ባሻገር ቤ/ክ እንጀራቸውን የምትሰጣቸው ቀሳውስት፤ ዲያቆናት፣ ዘማሪያን፣ ሰባኪያንና ለማኞችም እንዲኖሩ አድርጓል፡፡ አማኞችን ፈጥሯል፤ አማኞችም ከኪሳቸው ብርና ወርቅ እያወጡ እንዲለግሱ አድርጓቸዋል፡፡ የሰይጣን መኖር አማኞች ከእግዚአብሔር ጋር እንዲጣበቁ ቄሶችም በህብረተሰቡ ውስጥ ተሰሚ እንዲሆኑ አድርጓቸዋል፡፡”
ሰይጣን ከሌለ እግዚአብሔርም አስፈላጊነቱንና ምንነቱን ያጣል፡፡ እናም ቅድስት ክርስቶስ ሳምራ በየዋህነት ሰይጣንን ከእግዚአብሔር ጋር ለማስታረቅ ባደረገቸው ሙከራ ውስጥ እግዚአብሔር በሰዎች ውስጥ የነበረውን አስፈላጊነት ልታሳጣው ነበር፡፡
ቅድስት ክርስቶስ ሳምራ የሰይጣንን እምቢተኝነት መሰረት አድርጋ፣ ሄራክላይተስ ደግሞ የቅራኔዎችን ትግልና አንድነት ህግ መሰረት አድርጎ እግዚአብሔር ለሰይጣን ምህርት ማድረግ እንደማይችል አይተናል፡፡ ምንም እንኳን በእነዚህ ሁለት እሳቤዎች መሰርት እግዚአብሔር ለሰይጣን ምህረት ማድረግ ባይችልም እሳቤዎቹ የእግዚአብሔርንና የሰይጣንን ሕልውናን ግን አልካዱም፡፡ የዘመናችን ኢ-አማኒዎችም እግዚአብሔር ሰይጣንን መማርም ሆነ ማጥፋት አይችልም ብለው ቢያምኑም፤ ለዚህ እምነታቸው የሚያቀርቡት አመክንዮ ግን የሰይጣንንም ሆነ የእግዚአብሔርን ህልውና ሳይቀር የሚሞግት ነው፡፡
እንደ ኢ-አማኞች እሳቤ ሰይጣን የሚባል ራሱን የቻለ ህልውና ባህሪ፣ መልክና አካል ያለው ነገር በጭራሽ የለም፡፡ እግዚአብሔርም ሰይጣንን መማርም ሆነ ማጥፋት የማይችለው በሰይጣን እምቢተኝነትና ክፉ ባሕሪ የተነሳ ሳይሆን፣ ሁለቱም በእኛ ሕይወት ውስጥ ያሉና በአእምሯችን ውስጥ የሚፈጠሩ የቅራኔ ሃሳቦችና ስሜቶች በመሆናቸው ነው፡፡ ስለሆነም ክፉን በጥሩ፣ በሽታን በጤንነት፣ ጨለማን በብርሃን፣ ሞትን በህይወት፣ ጥላቻን በፍቅር ማሽነፍ ይቻል እንደሆነ እንጂ ማጥፋት ግን አይቻልም፡፡ ሃይማኖቶች ሰይጣንን “በማጥፋት” ላይ ሳይሆን “በማውገዝ” ላይ የተመሰረተ እምነት የፈጠሩት ለዚህ ነው፡፡ እነዚህ ሃይማኖቶች የሰውን ልጅ በገሃነመ እሳት በማስፈራራትና በተደራጀ ማህበራዊ ተቋም ሰይጣንን ለማውገዝ መታገላቸው የሚያሳየው በርግጥ “ሰይጣን” የሚባል ነገር መኖሩን ሳይሆን የሰውን ልጅ የሞራል ደረጃ ለማሳደግ ያደረጉን ጥረት ብቻ ነው። በማለት ይከራከራሉ
ክርስቲያኖች ፈላስፎች ደግሞ "በዓለም ላይ የሚፈጠረው ችግር በሙሉ ከአምላክ አፈጣጠር ክፍተት አሊያም ፍጹም መልካም ስላልሆነ ሳይሆን፣ ፍጡሮቹ ነጻ ፍቃዳቸውን አለአግባብ በመጠቀማቸው ነው የሚል መከራከሪያ ያነሳሉ
እንደ ኦገስቲን ያሉ ክርስቲያን ፈላስፎች "እግዚአብሔር ለአንዳንድ ፍጡራን ነጻ ፍቃድ እና እውቀት ሰጥተቸዋል፤ ታዲያ እግዚሃብሄር እንዲህ አድርጎ የፈጠራቸው ከራሳቸው የተነሳ የሚፈፅሙት መልካም ድርጊት ኹሉ በስማቸው እንደሚዘገብ በመፈለጉ ነው። "
ይህም ማለት "ነፃ ፍቃድን ለሰዎች እና ለመላእክት( ሴጣንን ጨምሮ) አጎናፅፎ ፤ መልሶ መጥፎ ነገር እንዳይሰሩ ክልከላ ማድረግ አለበት ማለት ምክንያታዊ አይደለም" ይሉናል
አሜሪካዊ ፈላስፋን ፕላቲንጋን
ለምን ይሆን ነጻ ፍቃድ የተሰጠን ብላቹ ብትጠይቁት “መልካም እና ሰናይ የሆነ ተግባር ልንፈጽምበት'' የሚል ምላሽ ይሰጣቹዋል ። ይህን ስጦታ ብንጠቀምበት ኖሮ ምድር ላይ መልካም ነገሮች ብቻ በሰፈኑም ነበር ይላል።
እናንተም ቀጥላቹ ለምን መልካም ነገር ብቻ በምድራችን ላይ ሳይገኝ ቀረ ብትሉት፣ “አሳዛኙ ነገር እነዚህ ፍጡራን የተሰጣቸውን ነጻ ፍቃድ ክፉውን ለመፈጸም መጠቀማቸው ነው፡፡
ፈጣሪ እነዚህን ፍጡራንን ነጻ ፍቃድ እንዲኖራቸው አድርጎ ቢፈጥራቸውም ሁሌም ሰናዩንና መልካሙን ብቻ እንዲተግብሩ ብቻ ግን አላደረገም፡፡ በፍቃዳቸው ተመርኩዘው መልካሙን እንዲያደርጉ አድርጎ እንደፈጠረ ኹሉ ክፉ የሆነ ተግባራትን (Morally evil) ሊፈጽሙ የሚችሉ ፍጡራንም በዛው ልክ እንዲፈጠሩ ፈቅዷል፡፡ ኾኖም ልብ ማለት ያለባቹ ክፉውን ሰዎች ከነጻ ፍቃደቸው የተነሳ መምረጥ እንዳይችሉ አላማድረጉን ነው” የሚል መልስ አለው ፕላንቲጋ፡፡
@zephilosophy
በእርግጥ “ሰይጣን” የሚባል ነገር አለ?
የአማኝ ና የኢ-አማኝ ሙግት
ፀሀፊ - ብሩህ አለምነህ
በጣም በርካታ ሃይማኖቶች ሰይጣንን በማውገዝ ላይ የተመሰረተ እምነት አላቸው፡፡ የእነዚህ ሃይማኖቶች ተከታዮችም ሰይጣን የሚባል የራሱ ህልውና ያለው አካል በዚህ ዓለም ላይ እንዳለ ያምናሉ፡፡ ይህ አቋም የእነዚህ ሃይማኖቶች ዋነኛ ምሰሶ ነው፡፡ ማንኛውም አማኝ ሰይጣን እንዳለ ማመን አለበት፡፡ ሰይጣን ሰዎችን ወደ ክፋት፣ ሃጢያትና ጥፋት ይወስዳቸዋል ተብሎ ስለሚታመን ይወገዛል፣ ይጠላል፤ በስዕል ላይም ጥቁር፣ አስቀያሚ፣ እሾሃማና ጨካኝ ተደርጎ ይሳላል፡፡
አሁን አሁን ግን በተለይ ከስነልቦናና ከህክምና ሳይንስ እድገት ጋር ተያይዞ በሰይጣን መኖር ላይ ጥርጣሬያቸውን መሰንዘር የጀመሩ ሰዎች በቁጥር እየበዙ ነው፡፡ ከዚህ ጥርጣሬያቸውም በመነሳት ብዙ ሰዎች በዓይን የማይታይ ክፉ መንፈሳዊ አካል አለ ብሎ ማመን ከብዷቸዋል፡፡ በዚህም የተነሳ የሰይጣንን ህልውና የሚጠራጠሩ በሂደት ሁለት ዓይነት የአመለካከት ጎራዎች ተፈጥረዋል፡፡ በመጀመሪያው ጎራ ውስጥ ያሉ ሰዎች ኢ-አማኒዎች (Atheists) ሲሆኑ፤ እነሱም እግዚአብሔርም ሆነ ሰይጣን የሚባል መንፈሳዊ አካል በጭራሽ የለም በማለት በግለጽ የኢአማኒነት አቋም የያዙ ናቸው፡፡
በሁለተኛው ጎራ ውስጥ ያሉ ሰዎች ግን አማኞች ናቸው፡፡ እዚህ ጎራ ውስጥ ያሉ ሰዎች በእግዚአብሔር መኖርና በአምልኮተ እግዚአብሔር የሚያምኑ ቢሆኑም ሰይጣንና ሲኦል አለ ብለው ግን አያምኑም፡፡
“እንዴት ያለ ልክ የሰውን ልጅ የሚያፈቅር አምላክ ሰዎች ላይ የሚጨክንና ክፉ የሆነ መንፈስ ፈጥሮ ያሰቃያቸዋል? ይሄ ነገር ከፈጣሪያችን ከእግዚአብሄር ሊሆን አይችልም፤” ብለው የሚያምኑ ክርስቲያኖች አሉ። እንደነሱ አመለካከት ከስጋችን ምኞት የሚመነጭ ፍላጎት ፣ ስሜትና ሀሳብ ሁሉ መፅሀፍ-ቅዱስ ውስጥ ሰይጣን ተብሎ ተፅፏል እንጂ ራሱን የቻለ ክፉ መንፈስ አይደለም ብለው ያምናሉ።
ክርስትያን ያልሆኑና ራሳቸውን በግልፅ የለዩ
እንደ ኢ-አማኒዎች አመለካከት እግዚአብሔር ከሰይጣን ጋር እንዳወራ የሚናገረው የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ አንድ መሰረታዊ ችግር አለበት፤ (የእዮብ ታሪክ) ይኼውም ይሄ ጥቅስ ከእግዚአብሔር መሰረታዊ ባህሪ ጋር የሚቃረን መሆኑ ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚለው አማኞችም ከልባቸው እንደሚያምኑት እግዚአብሔር መንፈስ በመሆኑ የቦታና የጊዜ ገደብ የለበትም፤ በእኛ ውስጥም (ልብና ኩላሊት እየመረመረም) ሆነ ከእኛ ውጭ ባለው ቦታና ጊዜ ውስጥ ሁሉ በምልዓት ይኖራል፡፡ በመሆኑም እግዚአብሔር የሌለበት ቦታና ጊዜ ዩኒቨርስ ውስጥ የለም፡፡ እንግዲህ እግዚአብሔር በሁሉም ቦታና ጊዜ ውስጥ ነዋሪ ከሆነ ሰይጣን በየትኛው ቦታና ጊዜ ውስጥ ሆኖ ነው ከእግዚአብሔር ጋር የሚያወራው? ለዚህ ጥያቄ ክርስትያኖች መልስ የላቸውም፡፡
በሁሉም ቦታና ጊዜ ውስጥ ሰፍኖ የመገኘት የእግዚአብሔር ባሕሪ ሰይጣንን የሚኖርበት የቦታና የጊዜ አውታር ያሳጣዋል፡፡ ምክንያቱም እነዚሁ አማኞች እንደሚሉት እግዚአብሔርና ሰይጣን በቦታና በጊዜ አንድ ላይ እንዲኖሩ የሚያስችል ተፈጥሮዊ ባህሪ ስለሌላቸው
ሌላው እግዚአብሔር ባለበት ቦታና ጊዜ ውስጥ ሰይጣን ሊኖር አይችልም እንዲሁም ሰይጣን ባለበት ቦታና ጊዜ ውስጥ እግዚአብሔር አይኖርም ችግሩ ግን እግዚአብሔር የሌለበት ቦታና ጊዜ (ዘመን) አለመኖሩ ነው።
ሰይጣን የሚባልም ነገር የለም የሚያስብለንም ይሄው የእግዜር በሁሉም ቦታና ዘመን የመገኘት ባህሪ ነው፡፡ እግዚአብሔር በሁሉም ቦታና ዘመን(ጊዜ) የሚኖር ከሆነ ደግሞ ሰይጣን ለአፍታ እንኳን የሚኖርበት ቦታና ጊዜ አይኖረውም፡፡
በዚህ አመክንዮ መሰረት ሰይጣን የሚባል ነገር አይኖርም፡፡ ሆኖም ግን ለዚህ አመክንዮና ሙግት እንደ ግሪጎሪ ጋንስለ ያሉ ክርስትያን ፈላስፎች ደግሞ የሚከተለውን አጸፋ ይሰጣሉ፣
“ቦታና ጊዜን የሚይዝ ነገር ሁሉ ቁሳዊ አካል ነው፤ መንፈስ ቁሳዊ አካል ባለመሆኑ ቦታና ጊዜን አይዝም፡፡ እግዚአብሔርም መንፈስ በመሆኑ ቦታና ጊዜን አይዝም፡፡ በመሆኑም እግዚአብሔር ከዚህ ዓለም ውጭ የሚኖር፣ ዩኒቨርስ በሚኖርበት የቦታ-ጊዜ አውታር ውስጥም የሌለ መንፈሳዊ አካል ነው፡፡
በመሆኑም እግዚአብሔር በዚህ ዓለም ላይ የለም፡፡ እንደነዚህ ክርስትያን ፈላስፎች አመለካከት እግዚአብሔር በሁሉም ቦታና ጊዜ ውስጥ አለ ማለት በቦታና በጊዜ ውስጥ ሁሉ የሞላ አካል አለው ማለት ሳይሆን፤ እግዚአብሔር የተመጠነ ረቂቅ መንፈሳዊ አካል ኖሮት ሆኖም ግን ሁሉንም ቦታዎችና ጊዜያት ሁሉ በርቀት የሚመለከት፣ ተጽዕኖ ማድረግ የሚችልና የሚቆጣጠር ነው ማለት ነው፡፡ በዚህ የአማኝ ፈላስፎች መከራከሪያ መሰረት እግዚአብሔር መንፈስም ቢሆን መንፈሳዊ አካሉ ግን ከቦታ ጊዜ አውታር ውጭ ነው፡፡ ይሄንን የእግዚአብሔር ባህሪ በፀሐይ ብርሃንና ሙቀት መስለን ማስረዳት እንችላለን፡፡
ፀሐይ ስትወጣ በሁሉም ቦታዎች ላይ የሚደርስ ብርሃንና ሙቀት አላት፡፡ ሆኖም ግን የፀሐይ ብርሃንና ሙቀት በሁሉም ቦታዎች ላይ መገኘታቸው፣ ፀሐይ በአካል በሁሉም አካባቢዎች ላይ ትገኛለች ማለት አይደለም፡፡ ፀሐይ በቦታ የተወሰነ አካል ቢኖራትም ብርሃኗና ሙቀቷ ግን በሁሉም ቦታዎች ላይ ሞልቶ ይገኛል፡፡ እግዚአብሔርም እንዲሁ ነው፤ መንፈሳዊ አካሉ በቦታ የተወሰነ ሆኖ ኃይሉ፣ ተፅዕኖውና ቁጥጥሩ ግን በሁሉም ስፍራዎችና ጊዜዎች ሁሉ የሞላ ነው፡፡
ጥያቄው ግን ክርስትያኖች የሚያምኑት ልክ ክርስትያን ፈላስፎች እንደሚከራከሩት እግዚአብሔር በዚህ ዓለም ላይ የለም ብለው ነው ወይ? የሚለው ነው፡፡ ኢ-አማኞች የሚሉትም፣
“ይሄ የክርስትያን ፈላስፎች መከራከሪያ በየዋህነት እግዚአብሔርን ከሚያመልኩ ክርስቲያኖች እምነት ያፈነገጠና በክርክሩ መፈናፈኛ ሲያጡ ለማምለጫ የፈጠሩት ሀሳብ ነው፤ ” በማለት ሀሳቡ ከመፅሀፍ ቅዱስ ጋር በግልፅ እንደሚጋጭ ያሳያሉ
ይቀጥላል .....
@zephilosophy
" ጥበብ " በተሰኙት ተከታታይ ቅጽ ባላቸው የፍልስፍና መጻሕፍቱ የምናውቀው ኃይለጊዮርጊስ ማሞ ( ጲላጦስ ) " ዝምታ " የተሰኘ ምርጥ መጽሐፍ ለንባብ አቅርቧል::ገዝታችሁ እንድታነቡት ጋብዘናችኋል
Владелец канала не предоставил расширенную статистику, но Вы можете сделать ему запрос на ее получение.
Также Вы можете воспользоваться расширенным поиском и отфильтровать результаты по каналам, которые предоставили расширенную статистику.
Также Вы можете воспользоваться расширенным поиском и отфильтровать результаты по каналам, которые предоставили расширенную статистику.
Подтвердите, что вы не робот
Вы выполнили несколько запросов, и прежде чем продолжить, мы ходим убелиться в том, что они не автоматизированные.
Наш сайт использует cookie-файлы, чтобы сделать сервисы быстрее и удобнее.
Продолжая им пользоваться, вы принимаете условия
Пользовательского соглашения
и соглашаетесь со сбором cookie-файлов.
Подробности про обработку данных — в нашей
Политике обработки персональных данных.