ፍልስፍና እውነትን በመፈለግ- ልማዳዊ እምነቶችን በመሞገት እና ጭፍን አመለካከቶችን በጥበብ በመመርመር ወደ ላቀ አሰተሳሰብ ያሻግራል።
በዚህ ቻናል አለም ላይ ያሉ ፍልስፍናዎች ፤ ርዕዮት አለሞች ፤ ሀይማኖቶች እና አስተሳሰቦች በነፃነት ይዳሰሳሉ።
Информация о канале обновлена 17.08.2025.
ፍልስፍና እውነትን በመፈለግ- ልማዳዊ እምነቶችን በመሞገት እና ጭፍን አመለካከቶችን በጥበብ በመመርመር ወደ ላቀ አሰተሳሰብ ያሻግራል።
በዚህ ቻናል አለም ላይ ያሉ ፍልስፍናዎች ፤ ርዕዮት አለሞች ፤ ሀይማኖቶች እና አስተሳሰቦች በነፃነት ይዳሰሳሉ።
ስለ ፍትህ
1."ህግ ታናናሽ ሰዎችን ሲገዛ ፣ ስነ-ምግባር ደግሞ ታላላቅ ሰዎችን ይገዛል።"
አቡነ ሺኖዳ
2."ግማሽ እውነት ሙሉ በሙሉ ሀሰት ነው።"
እስራኤሌያውን
3."የብልህ ሰው ህግ የህይወት ምንጭ ናት። ማስተዋል የሌለው ግን በኀጢአት ይሞታል ።"
ምሳሌ 13:14
4."ብዙዎቹ ሀይማኖቶች ያስቀመጧቸው መመሪያዎችና ደንቦች ገነት ለመግባት ጉቦ የመክፈል ያህል ነው።"
ጲላጦስ
5."የሁሉም መብቱ በፍርድ ቀን ይመለስለታል ፣ ቀንድ የሌለው በግ እንኳን ከወጋው ቀንዳም ወጠጤ ላይ ካሳውን ይቀበላል።"
ነብዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ)
6."ወንድሜ ሆይ ሳይፈረድብህ በራስህ ላይ ፍረድ"
መርቆርዮስ
7."መልካም መስራትን ተማሩ ፣ፍርድን ፈልጉ ፣ የተገፋውን አድኑ ፣ ለተበዳዩ ፍረዱለት ፣ ለመበለቲቱ ተሟገቱ "
ኢሳ ፤ 1፣17
8."ትክክለኛ ፍትህ የሌለበት የመንግስት አስተዳደር ፣ የራስ ወዳድ ግለሰቦችና የአድርባዮች መሰብሰቢያ ካንምኘ ይሆናሉ።"
በላይ ደስታ
9."በጎረቤት ላይ ፍትህ ሲጓደል እያየህ ዝም ካልክ ፣ ቀጣዩ ተረኛ አንተ መሆንህን አትዘንጋ።"
ሞገስ በላቸው
10."በስንፍና ከሚፈርዱ ፈራጆች ጩኸት ይልቅ የጠቢባን ቃል በጸጥታ ትሰማለች።"
መክ፤ 9:17
@zephilosophy
📚Thus Spoke Zarathustra
Friedrich Nietzsche (Author),
Adrian Del Caro (Translator)
ዘስ ስፔክ ዛራቱስትራ የተሰኘው በጥልቅ የኤግዚስተንሺያል ፍልስፍና ይዘቱ በዓለም በመጀመሪያዎቹ ተርታ የሚጠቀስ ድንቅ መፅሐፍ ነው። እንደሚታወቀው ይህ መፅሀፍ በዝነኛው ደራሲና ፈላስፋ - በፍሬደሪክ ዊልሄልም ኒቼ በጎርጎሮሳውያኑ ዘመን አቆጣጠር በ1880ዎቹ መጀመሪያ የተፃፈና የታተመ ነው።
ከተፃፋበት ጀርመንኛ ወደ እንግሊዝኛ የተተረጎመው ኮፒ - "ዘስ ስፖክ ዛራቱስትራ" - በዓለም በስፋት ከተሠራጩ የፍልስፍና ነክ መፅሐፎች ቀዳሚውን ሥፍራ ይይዛል።
@Zephilosophy
@Zephilosophy
ወሬኞችና ወሬያቸው ሰልችተውኛል፤ ነፍሴ ተፀይፋቸዋለች፡፡ …የማየው ነገር ሁሉ በግብዝነት የተሞላ ትርጉም አልባ የወሬ ቋት ነው፡፡
ከአንድ ጓደኛዮ ጋር ቁጭ ብል አቶ ወሬ ሳይጋበዙ ይቀላቀላሉ፡፡ በዘዴ ላታልላቸው ብሞክር እንደምንም ይቀርቡኝና በድምፃቸው ማሚቱ ዕረፍት ይነሱኛል፣ እንደ በሰበሰ ስጋ ጨጓራየን ያውኩታል፡፡ …ወፍራም ከናፍራቸውን እየከፈቱ ሲለፈልፉ አገኛቸዋለሁ፡፡ አጃቢዎቻቸውም ለእሳቸው ያጨበጭቡላቸዋል፣ በእኔ ይሳለቁብኛል፡፡
በባዶ ወሬ ውስጥ ግርግር የማይኖርበት ስፍራ ይኖር ይሆን?
በዚህ ምድር ራሱ ቢያወራ የማይወድ ሰው ይኖር ይሆን?
ከዚህ ሁሉ ሕዝብ መሃል አፉ ለወስላታው አቶ ወሬ መሸሸጊያ ያልሆነ ይገኝ ይሆን?
አንድ አይነት ወሬኞች ብቻ የሚገኙ ከሆነ እኔ እረታለሁ፡፡ ነገር ግን ወሬኞች በቁጥር የሚያዳግቱ ናቸው፡፡ በጎሳና በቡድን ሊከፈሉም ይችላሉ፡፡ … አንዳንድ ጊዜ ራቁታቸውን ከነፈሰው ጋር የሚነፍሱ ወሬኞች የተሰበሰቡበት ቡድን እናገኛለን፡፡ ብዙውን ጊዜ አንድ የተለየ መዋቅር ያለው ቡድን እናገኛለን፡፡ የዚህ ቡድን ወኪሎች ልክ እንደ ወፎች ቢሆኑም በቃላቶቻቸው ሞገድ ውስጥ ሲፈስሱ ግን ራሳቸውን እንደ ንስሮች ይቆጥራሉ፡፡
ሌሎችም ወሬኞች አሉ፤ በደወል ድምፅ የሚመሰሉ፡፡ ሰዎችን ወደ አምልኮ ሥፍራ የሚጠሩ ቢሆንም ራሳቸው ወደ ቤተ ክርስቲያን ዝር ብለው አያውቁም፡፡
…ከእነዚህ ሁሉ ግን በእኔ አስተሳሰብ አስገራሚዎች የሚመስሉኝ በሚያንኮራፋ ድምፃቸው ዓለምን የሚያውኩና ከጊዜ ወደ ጊዜ ራሳቸውን እያነቁ "እንደ እኛ ሊቅ የት ይገኛል!” የሚሉ እንቅልፋሞች ናቸው፡፡
ለአቶ ወሬና ለጓደኞቻቸው ጥላቻዮን ከገለፅኩ በኋላ ራሴን ልክ ራሱን ማዳን እንደማይችል ሐኪም ወይም ለእስር ቤት ጓደኞቹ እንደሚጸልይ እስረኛ ሆኘ አገኘዋለሁ፡፡ አቶ ወሬንና ወሬኛ ጓደኞቻቸውን በራሴ የወሬ መንገድ በምፀት ተችቻቸዋለሁ፡፡ ከወሬኞች የተነጠልኩ ብሆንም እኔ ራሴ ወሬኛ ነኝ፡፡ እግዚአብሔር እኔን ባርኮ ወሬኞች በማይኖሩበት የዕውቀት፣ የእውነትና የፍቅር ዓለም ከማስቀመጡ በፊት ሃጢአቴን ይቅር ይለኝ ይሆን?
ካህሊል ጅብራን
📖የጠቢባን መንገድ
@Zephilosophy
አንድ ሰው ማሃቪራን እንዲህ ሲል ጠየቀው፡-
እውነተኛ ቅዱስ ማን ነው?
እና ማን ነው ጥፋተኛ?
ምናልባት ጠያቂው በሃይማኖታዊ ጽሑፎች ውስጥ የሚሰጠውን ዝግጁ የሆነ መልስ ፈልጎ ሊሆን ይችላል፣ ነገር ግን እንደ ማሃቪራ ያሉ ሰዎች ከራሳቸው ነባራዊ ግንዛቤ ነው የሚናገሩት። የተናገረው ነገር በጣም ያምራል። የሰጠው ፍቺ ልዩ ነው። በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ ምንም ተመሳሳይነት የለውም።
ማሃቪራ እንዲህ ብሏል፦
የነቃ ቅዱስ ነው።
የሚተኛው ኃጢአተኛ ነው።
ቀላል ፣ ግን በጣም አስፈላጊ…
"ንቃት" ያለው ብቸኛው ቅድስና ነው።እና ፤ንቃተ-ህሊና ማጣት ብቸኛው ኃጢአት ነው. ሌሎች ኃጢአቶች የሚመነጩት ከዚህ ካለማወቅ ነው። ሥሩን ይቁረጡ፤ ሥሩን ራሱ ይምቱ! ቅጠሉን አይቁረጡ።
ኦሾ
@Zephilosophy
@Zephilosophy
ያ ሁሉ የዕውቀት ፍሬ- የልጅነት ዓለም
ዝቆ የሰፈረው
ያ ሁሉ የዕውቀት ፍሬ -የልጅነት ጉጉት
አጣፍጦ የፈጠረው፡፡
ይኑር ምንም አይደል!
ምኞቶች ያፋፋል፣
በብርሃን ጽንፉ ጨለማን ይገፋል፣
ግን ልንገርህ አይደል?
እንደኔ የሆንክ ለት - ላይበቅል ይደፋል፤
ላይበላ ይረግፋል።
አዎ! እንደ እኔ የሆንክ ለት፣
ሁሉን ወደማወቅ የተቃረብክ ለት፤
ይሸረክትሃል፣
ይቆራርጥሃል -የእኩዮችህ ስለት፡፡
እውነቴን ነው የምልህ!
የዚህች ዓለም ቅኔ ግራ ነው ፣ ግራ ነው
'ሲፈቱት ይጠብቃል'፤
እያንዳንዱ እውነት በውሸት ይጠበቃል።
📖የመንፈስ ከፍታ
ገጣሚ -ሀፊዝ
@zephilosophy
ብዙ ተባዙ፣
ምድርንም ሙሏት
ከሆነ ትዕዛዙ፣
ምድሪቱ ሞልታለች፣
ከገደብ እንዳናልፍ፣
ትዕዛዝ እንዳንጥስ፣
ጎበዝ ፍሬን ያዙ፡፡
📖መደድ
ገጣሚ-ኑረዲን ዒሳ
@zephilosophy
Владелец канала не предоставил расширенную статистику, но Вы можете сделать ему запрос на ее получение.
Также Вы можете воспользоваться расширенным поиском и отфильтровать результаты по каналам, которые предоставили расширенную статистику.
Также Вы можете воспользоваться расширенным поиском и отфильтровать результаты по каналам, которые предоставили расширенную статистику.
Подтвердите, что вы не робот
Вы выполнили несколько запросов, и прежде чем продолжить, мы ходим убелиться в том, что они не автоматизированные.