ፍልስፍና እውነትን በመፈለግ- ልማዳዊ እምነቶችን በመሞገት እና ጭፍን አመለካከቶችን በጥበብ በመመርመር ወደ ላቀ አሰተሳሰብ ያሻግራል።
በዚህ ቻናል አለም ላይ ያሉ ፍልስፍናዎች ፤ ርዕዮት አለሞች ፤ ሀይማኖቶች እና አስተሳሰቦች በነፃነት ይዳሰሳሉ።
Информация о канале обновлена 17.11.2025.
ፍልስፍና እውነትን በመፈለግ- ልማዳዊ እምነቶችን በመሞገት እና ጭፍን አመለካከቶችን በጥበብ በመመርመር ወደ ላቀ አሰተሳሰብ ያሻግራል።
በዚህ ቻናል አለም ላይ ያሉ ፍልስፍናዎች ፤ ርዕዮት አለሞች ፤ ሀይማኖቶች እና አስተሳሰቦች በነፃነት ይዳሰሳሉ።
"እግዚአብሔር በሁሉም ነገሮች ውስጥ ካለ ሰይጣን የሚኖረው የት ነው?"
...የቀጠለ
ክርስትያን ፈላስፎች፣ “ሰይጣን ከእግዚአብሔር ጋር በቦታና በጊዜ
ከእግዚአብሔር ውስጥ ጎን ለጎን ይኖራል፤” የሚለውን መፅሃፍ ቅዱሳዊ አንደምታ ለመታደግ ሲሉ ብቸኛው ማምለጫ መንገዳቸው ከእግዚአብሔር ባህሪያት ላይ የተወሰነ ማሻሻያ ማድረግ ነው፤ ማሻሻያውም፣
“እግዚአብሔር መንፈሳዊ አካል እንዳለው፤ ሆኖም ግን ይህ አካሉ በተወሰነ ቅርጽ፣ አካልና ባህሪ እንደሚገኝና ዩኒቨርስንም የሚቆጣጠረው በርቀት (በሪሞት ኮንትሮል) ነው የሚል እንግዳ ሀሳብ አመጡ፤”
በማለት ይወቅሷቸዋል፡፡
ምንም እንኳን ክርስትያን ፈላስፎች እንዲህ እያሉ ቢራቀቁም መጽሐፍ ቅዱስ ግን በግልጽ፣
“ሰው በስውር ቢሸሸግ እኔ አላየውምን? ሰማይንና ምድርንስ የሞላሁት እኔ አይደለሁምን? ይላል እግዚአብሔር” (ኤር 23፤24) በማለት፤ እንዲሁም፣
“ወደ ሰማይ ብወጣ አንተ በዚያ ነህ፤ ወደ ሲኦልም ብወርድ በዚያ አለህ፡፡” (መዝ 138(139)፣8)
በማለት እግዚአብሔር ዓለምን የሚያየውና የሚቆጣጠረው በርቀት ሳይሆን ሁሉም ቦታ ላይ በአካል በመገኘት እንደሆነ በግልፅ ይናገራል፡፡
“እግዚአብሔርና ሰይጣን መንፈሳዊ አካሎች ስለሆኑ በቦታና በጊዜ የተቀነበበው ዩኒቨርስ ውስጥ አይኖሩም፤” የሚለውን የክርስትያን ፈላስፎችን ሃሳብ ብንቀበል እንኳን ይህ አስተሳሰብ ብዙም የማያራምድና ከመፅሐፍ ቅዱስ ጋርም በግልጽ የሚጋጭ መሆኑ አይቀርም፡፡
ምክንያቱም አንደኛ መፅሀፍ ቅዱስ ውስጥ “ሰይጣን የዚህ ዓለም ገዥ እንደሆነ” (ዮሐ 12፣31) እና በሰው ልጅ ላይም እንደሚሰፍር በግልጽ መናገሩ ነው፡፡ ሁለተኛ እግዚአብሔር ስራውን ለመስራት ዓለማዊውን ጊዜ መጠቀሙ ነው፤ ለምሳሌ መጽሐፍ ቅዱስ፣ “እግዚአብሔር ስራውን (ተዓምር) የሚሰራበት የራሱ ጊዜ አለው፤” ይላል፡፡ ሦስተኛ ክርስትያኖች እንደሚያምኑት አምላክ የሆነው ክርስቶስ በቦታና በጊዜ ውስጥ ተወስኖ በዚህ ዓለም ላይ መኖሩ ነው፡፡
በእነዚህ 3 መፅሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃዎች ምክንያት መንፈሳዊ
አካላት የሆኑት እግዚአብሔርና ሰይጣን እኛ በምንኖርበት ቁስ አካላዊ ቦታና ጊዜ ውስጥ አይኖሩም ብሎ መከራከር ብዙም አያዋጣም፡፡ ይሄ ከሆነ ደግሞ ክርስትያኖች እንደሚያምኑት እግዚአብሔር በርግጥም ከዩኒቨርስ ባሻገርም ሆነ በቦታ-ጊዜ አውታር ውስጥ ሁሉ በምልዓት የመኖሩ ነገር ግድ ይሆናል፡፡ ሆኖም ግን ይህ አስተሳሰብ ቀደም ብለን ወዳነሳነው በእግዚአብሔርና ሰይጣን ባህሪና ህልውና መካከል ወዳለው ስነ አመክኖያዊ ቅራኔ ይመልሰናል፡፡ ቀደም ብልን እንዳነሳነው ደግሞ የዚህ አስተሳሰብ መሰረታዊ ችግሩ ሰይጣን የሚኖርበትን ቦታና ጊዜ ማሳጣቱ ነው፡፡ እግዚአብሔር በሁሉም ነገሮች ውስጥ ካለ ሰይጣን የሚኖረው የት ነው?
አማኞች ሰይጣን ስለመኖሩ የሚያቀርቡት ሌላው መከራከሪያቸው በዚህ ዓለም ላይ የሚከሰቱት ወንጀሎች፣ ኢ-ሰብዓዊ ድርጊቶች፣ መከራዎችና ስቆቃዎች ማቆሚያ አለማግኘታቸውን ነው፡፡ እንደነሱ አስተሳሰብ ከእነዚህ አረመኔያዊ ድርጊቶች ጀርባ ሁሉ ዲያብሎስ የሚባል እርኩስ መንፈስ አለ፡፡ ይህ እርኩስ መንፈስ ሰዎችን ወደ ወንጀል፣ ወደ ውሸት፣ ወደ ሀጢያት፣ ስርቆት፣ ዝሙት፣ ሱስና ወደ ሌሎችም መጥፎ ባህርያት ያነሳሳቸዋል፡፡
“እሺ ይሁን ብለን ይሄንን የአማኞችን ሃሳብ ብንቀበል እንኳን ሌላ ጥያቄ ማጫሩ አይቀርም፤” ይላሉ ኢ-አማኒዎች:: “በዚህ ዓለም ላይ ለምናየው ክፋት፣ ሰቆቃና መከራ ተጠያቂው ሰይጣን ነው፤” ብለን ብናምን እንኳን እግዚአብሔር የሠውን ልጅ የሚወድና ሁሉን ቻይ ከሆነ ስለምን ሰይጣንን አያጠፋውም? ወደሚል ሌላ ጥያቄ ይወስደናል፡፡ ይህ ጥያቄ የጥንታዊ ግሪክ ፈላስፋ የሆነውን ኤፒኩረስንም ሆነ እንግሊዛዊውን ፈላስፋ ዴቪድ
ሂዩምን ያስገርማቸዋል፡፡ እውነት ግን ስለምን እግዚአብሄር ሰይጣንን አያጠፋውም?
“ምናልባት ግን እግዚአብሔር ሰይጣንን የማጥፋት ፍላጎት ቢኖረው እንኳን ይህንን ማድረግ አይችል ይሆን እንዴ? እንዲህ ከሆነ ደግሞ እግዚአብሔር ምኑን ሁሉን ቻይ ሆነው?! ወይም ደግሞ፣ እግዚአብሔር ሰይጣንን ማጥፋት ይችል ይሆናል፤ ግን ደግሞ ይሄንን ለማድረግ ፍላጎት ላይኖረው ይችላል፡፡ ይሄ ከሆነ ደግሞ እግዚአብሔር ራሱ መልካም አይደለም ማለት ነው፡፡ ግን ደግሞ ከእግዚአብሔር ሁሉን ቻይነትና የደግነት ባህሪ ተነስተን እግዚአብሔር ክፋትን ለማጥፋት ፍላጎቱም ችሎታውም አለው ካልን ይሄ ሁሉ ክፋትና አደጋ፣ ሰቆቃና ዋይታ እንዴት ሊኖር ቻለ? ብለን እንድንጠይቅ ያደርገናል።"
ይቀጥላል..
@zephilosophy
‹‹ሰው›› ከመሆን በላይ ምን አለ?
ፈላስፋ እና ደራሲው ካህሊል ጂብራን፡- ‹‹አንድ ሰው በውስጡ ሁለት ሰዎችን ነው፤ አንዱ በብርሃን ሲተኛ ሌላው በጨለማ ይነቃል›› አለ፡፡ በዛሬዋ ኢትዮጵያ የብዙዎች ማንነት እንዲሁ መስሏል። በብርሃን የሚተኛ ማንነት የሰው ስላም ይረብሸዋል፣ የሰው ፍቅር ያውከዋል፣ የሰው አንድነት ይበታትነዋል፣ የሰው መከባበር ዝቅ ያደርገዋል፣ የሰው ሳቅ ያስለቅስዋል፣ የሰው ዝምታ ያስጮኸዋል፡፡ እናም በብርሃን መተኛትን ይመርጣል።
በጨለማ ደግሞ ይነሳል፡- ስለጦርነት ይሰብካል፣ ስለብሔሩ ይፎክራል፣ ስለመንደሩ ይጮሃል፣ ስለዕልቂት ይተነብያል፡፡ በእሱ ዘንድ ‹‹ሰው›› የለም፡፡ ለእሱ ህያው የሚላቸው ነገሮች በደቦ የሚታሰቡበቱ ፓርቲው፣ ብሄሩ፣ እምነቱ ወይም ደግሞ ቡድኑ ናቸው፡፡ እነሱ መልካም የሚሉት መልካም፣ ክፉ የሚሉትንም ክፉ ብሎ እያስተጋባ ይቀጥላል፡፡ "ሰው መሆንን" ብቻ ይዘው የዕውቀት ጫፍ የረገጡት ለሰው ጥቅም በፈጠሩት ቴክኖሎጂ ሰውን ሲያክፋፋ፣ ሲያጥላላ፣ ሲሳደብና ሲራገም ውሎ ይገባል።
ዛሬ ሰውን ከሰው በሚያማርጥ እና በሚያበላልጥ የብሄር ማንነት፣ የፖለቲካ አቋም፣ የሀብት መጠን የሃይማኖት ፍልስፍና እና የፍትህ ትርጉም ተይዘን የሰዎችን ተፈጥሯዊ እኩልነት እስከመዘንጋት ደርሰናል።
ጠቢቡ ዲዮጋን በቀን ብርሃን ፋኖስ አብርቶ በገበያ ሥፍራ ሲዞር የተመለከቱት ምን እንደሚፈልግ ሲጠይቁት፡- ‹‹ሰው እየፈለግሁ ነው›› አላቸው። ሰው በሞላበት ሀገር ‹‹ሰው›› መፈለግ ግዴታ የሚሆንበት አንዳንድ ዘመን አለ፡፡ የዲዮጋን ዘመኗ አቴና የሰው ትርጉሙ እንጂ የሰው እውነቱ የጠፋባት መስላ ነበር። አንዱ በዘሩ፣ ሌላው በዕውቀቱ፣ ከፊሉ በዝናው፣ ግማሹ በሀብቱ፣ የቀረውም በሃይማኖቱ የማንነቱን ትርጉም እየገለጠ ‹‹ሰው›› መሆንን ወደ ትንሽነት ቀየረው᎓᎓ ሰው መሆን ለዘረኛውም፣ አዋቂ ነኝ ለሚለውም፣ በሀብቱ ለሚመካውም፣ በዝናው ለሚኮፈሰውም፣ በእምነቱ የፅድቅ አክሊል ለጨበጠውም ዋጋ ቢስ ነበር፡፡ ዲዮጋን ስዎችን በትዝብት ሲመለከት ሰው መሆናቸውን ረስተዋል፤ ለእነሱ የሰው ዋጋ መተመኛው ሆኖ የሚያለያያቸው፣ የሚያጋድላቸው በእሱ ዘንድ እጅግ የተዋረደ ቢሆንበት ተደነቀ፡፡ የሰው መሆንን ትልቅነት በዘነጉ ሰዎች መካከል ራሱን ቢያገኘው ‹‹ሰው›› ፍለጋ ወጣ፡፡ በሁሉም ላይ ከሚወጣው የቀኑ ብርሃን ይልቅ ዲዮጋን በፋኖሱ ጭላንጭል ‹‹ሰው›› እንደሚያገኝ አምኗል፡፡ እኔም አንዳንዴ ሰው ከመሆን ባሻገር በሌላ ተቀጥላ ስምና ማንነት የማያምን ‹‹ሰው›› (እንደ ዲዮጋን) መፈለግ ይናፍቀኛል፡፡
የእኛ ፖለቲካ ‹‹ሰው›› አያውቅም፡፡ በብሄር፣ በጎሳና፣ በቡድን እንድታስብ ለሚሻ ፖለቲካ ሰው ‹‹ምንም›› ነው፡፡ ግለሰባዊ እምነትና አስተሳሰብ ቦታ አይሰጠውም፡፡ አሻፈረኝ ብለህ እንደሰው ለሚገባህ ሥፍራ ብትቆም እንኳን በቡድን ሃሳብ ትጨፈለቃለህ፡፡
የእኛ እምነት ‹‹ሰው›› አያውቅም፡፡ ዛሬ በኢትዮጵያ የአማኝ እንጂ የእምነት ተቋማት ችግር የለም። የእኛ አማኝ በጥላቻ፣ በነቀፌታ እና በራስ ፍቅር የተጠመደ ነው፡፡ ለእኛ ሀገር አማኝ ‹ሰው›› መሆንህ ብቻ አይበቃውም፡፡ እሱ የሚያምነውን ማመን፣ እሱ የሚከተለውን መከተል፣ የእሱን ቋንቋ መናገር ካልቻልክ ‹‹ሰው›› ብቻ ብትሆን ምን ያደርግለታል? የቱንም ያህል ጥሩ እና በጎ አድራጊ ሰው ልትሆን ትችላለህ፤ እንደምትከተለው ሃይማኖት የሰማይ ዋጋህን በየጓዳቸው ይወስኑልሃል እንጂ በአንተ አይቀኑም። በአደባባይ ደግሞ ‹‹ተቻችሎ የመኖር ባህል›› ይሉታል፡፡ ሰውን እንደ ‹‹ሰው›› በእኩል የሚመለከት እምነት ቢኖረንማ ተቻችሎ መኖር ቀድሞውንም ባልተደሰኮረ ነበር።
በመጨረሻም እንዲህ _ እላለሁ፡- ‹‹ማንንም _ ሰው ጌታው እንዲሆን የማይፈቅድ እና እሱም የማንም ሰው ጌታ መሆን የማይሻ በእርግጥ እሱ ታላቅ ሰው ነው››፡፡
መፅሀፍ- ዝምታ
ደራሲ-ኃይለጊዮርጊስ ማሞ
@zephilosophy
" ጥበብ " በተሰኙት ተከታታይ ቅጽ ባላቸው የፍልስፍና መጻሕፍቱ የምናውቀው ኃይለጊዮርጊስ ማሞ ( ጲላጦስ ) " ዝምታ " የተሰኘ ምርጥ መጽሐፍ ለንባብ አቅርቧል::ገዝታችሁ እንድታነቡት ጋብዘናችኋል
ግንዛቤ
ሳድጉሩ
“ግንዛቤ” ለተለያዩ ሰዎች የተለያዩ ነገሮች ማለት የሆነና ግልጽ ያልሆነ ቃል ነው። “ግንዛቤ” ስትል ከአእምሮ ንቃት ጋር እንዳታምታታው። የአእምሮ ንቃት በተሻለ ሁኔታ ለመኖርና የመኖርህን ሂደት በትንሹ ከፍ ባለ መንገድ እንድትመራ ይረዳሀል፡፡ ግንዛቤ አንተ የምታደርገው ነገር አይደለም፤ ሕያውነት ነው። የአንተ ሕያውነትህ በአንተ ግንዛቤ ምክንያት ብቻ ነው᎓᎓ ሙሉ በሙሉ ግንዛቤ የሌለህ ከሆንክ ህያው መሆንህን አታውቅም፡፡ በሕይወት የምትኖረው ባለህ ግንዛቤ መጠን ብቻ ነው። የግንዛቤህ መጠን የሚለካው ደግሞ፣ አንድ ነገር በተሞክሮህ ውስጥ ባለው መጠን ነው፡፡
“ግንዛቤን መለማመድ የምችለው እንዴት ነው?” ብለህ ትጠይቅ ይሆናል፡፡ ግንዛቤን መለማመድ አትችልም፡፡ ሕይወትንስ እንዴት መለማመድ ትችላለህ? አሁን ለምታስበውና ለሚሰማህ ነገር ትልቅ ቦታ የምትሰጥ ከመሆንህ የተነሳ፣ ለህያውነትህ ብዙ ቦታ አትሰጥም፡፡ የስነ ልቦና ሂደትህም ከሕይወት ሂደትህ የበለጠ አስፈላጊ ሆኗል። አእምሮህ ጫጫታ ውስጥ ባይሆን፣ ግንዛቤ ተፈጥሯዊ መንገድ ነበር፧ ነገር ግን አእምሮህ ማለቂያ ወደሌለው ሁካታ ውስጥ እንዲገባ ስላደረግክ ግንዛቤ ከባድ የሆነ ይመስላል፡፡
ሰዎች የአስተሳሰባቸውን ሂደት በጣም አስፈላጊ ከማድረጋቸው የተነሳ “አስባለሁ፤ ስለዚህም አለሁ” እስከማለት ደርሰዋል፡፡ ግን እውነቱ የትኛው ነው፤ የምታስበው _ ስላለህ ነው ወይስ ያለኸው ስለምታስብ ነው? ሀሳብ ማፍለቅ የቻልከው ስላለህ ነው፣ አይደል? በየትኛውም መንገድ በስነ ልቦና ሂደትህ መጫወት ትችላለህ፤ ነገር ግን ማሰብ የምትችለው ህያው ስለሆንክ ብቻ ነው፡፡ ህያው መሆን ከማይረባ የአስተሳሰብ ሂደትህ ይልቅ እጅግ ትልቅ ሂደት ነው።
ከፈለግክ ሙሉ በሙሉ መኖር፣ ግን አለማሰብ ትችላለህ። እንዲያውም ብታስተውል በሕይወትህ ውስጥ በጣም ቆንጆዎቹ ጊዜዎች ስለ ምንም ነገር ሳታስብ የቆየህባቸው ጊዜያት ናቸው። የደስታ ጊዜያት፣ የሀሴት ጊዜያት፣ ፍጹም የሆኑ የሰላም ጊዜያት... ብለህ የምትጠራቸው ጊዜያት ስለ ምንም ነገር ሳታስብ የኖርክባቸው ጊዜያት ናቸው፡፡
ታዲያ ይበልጥ አስፈላጊው የትኛው ነው፤ መኖር ወይስ ማሰብ? ህያው ፍጡር መሆን ትፈልጋለህ ወይስ የምታስብ ፍጡር? መወሰን አለብህ፡፡ አሁን ዘጠና በመቶ የሚሆነውን ጊዜ የምታሳልፈው ስለ ሕይወት በማሰብ እንጂ ሕይወትን በመኖር አይደለም፡፡ እዚህ የመጣኸው ግን ሕይወትን ለመለማመድ እንጂ ስለ ሕይወት ለማሰብ አይደለም፡፡ ሕይወትን መለማመድ ትፈልጋለህ፣ በሃሳብህ ከጠፋህ ግን ሕይወትን መለማመድ አትችልም፡፡ · ሕይወትን የምትለማመደው በስሜት ህዋሳትህ እንጂ በማሰብ አይደለም፡፡ ሃሳቦችህ ከእውነታው ጋር ምንም ግንኙነት የሌላቸው በመሆኑ የምታስበው ነገር ምንም ትርጉም የለውም፡፡ ማሰብ ከእውነታው ጋር ግን ምንም ግንኙነት ስለሌለው፣ ሁሉም ሰው በፈለገው መንገድ የራሱን የማይረባ ነገር ማሰብ ይችላል፡፡
የስነ ልቦና ሂደትህ ከሕይወት ሂደት ጋር ሲነጻጸር በጣም ትንሽ ክስተት ነው። አሁን አንተ ማሰብን በሕይወት ከመኖር በላይ አስፈላጊ እንደሆነ ስለምታስብ፣ ከአንተ ሃሳብ ጋር በጥቂቱም ቢሆን ብጋጭ ለእሱ ስትል ልትሞት እንኳን ፍቃደኛ ነህ። ሰዎች ለሀሳባቸው፣ ለሚያምኑበት ነገር ይሞታሉ፡፡ ሰዎች በሕይወት መኖር ማለት ምን ማለት እንደሆነ ስላላስተዋሉ ማሰብ ከሕይወት ሂደት የበለጠ አስፈላጊ ሆኗል። ሕይወት በመኖር እንቅስቃሴ ስለተዋጠ፣ ማሰብ ከሕይወት የበለጠ ታላቅ ይመስላል። ግን እንደዚያ አይደለም፡፡ _ አስተሳሰብ ከሕይወት ሂደት ጋር ሲወዳደር ትንሽ ክስተት ነው።
አርስቶትል የዘመናዊ አመክንዮ አባት ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ የእሱ አመክንዮ በጣም ቀላል እና ቀጥተኛ ነው A መሆን የሚችለው A ብቻ ነው፤ B መሆን የሚችለው B ብቻ ነው፡፡ A፣ B ሊሆን አይችልም፤ Bም A ሊሆን አይችልም፡፡ በዚህ መከራከር ትችላለህ? ምክንያታዊ በሆነ መልኩ ትክክል ይመስላል፡፡ ግን እስቲ ይህን እንይ፦
እዚህ ወንድ ወይም ሴት ሆነህ ተቀምጠሃል፡፡ ግን እንዴት ወደዚህ መጣህ? ሴት ነሽ እንበል፣ አባትሽ ለአንቺ መምጣት ምንም አላዋጣም ማለት ነው? በአንቺ ውስጥ አለ፣ አይደለም እንዴ? ወንድ ከሆንክም እናትህ ምንም አላዋጣችም ማለት ነው? እናትህ በአንተ ውስጥ የለችም? እውነት ነው አንተ ወንድ ወይም ሴት ነህ፤ ሀቁ ግን ሁለቱንም መሆንህ ነው፡፡ እውነት በምክንያታዊነት ሊገለጽ የማይችል ልኬት ነው፡፡ እውነት ከአመክንዮ ጋር አይገጥምም፤ ምክንያቱም አመክንዮ ሁልጊዜ የሚከፋፍል ሲሆን፣ እውነት ግን አንድ አድራጊ ነው፡፡ ታዲያ ይህ አመክንዮ ከሕይወት ጋር የሚገጥመው የቱ ጋ ነው?
የአንተን አመክንዮ በሕይወትህ ላይ ከልክ በላይ የምትተገብረው ከሆነ፣ ሁሉም ሕይወት ከውስጥህ ተጨምቆ ይወጣል። የአእምሮ አመክኗዊ ገጽታ የሚጠቅመው የሕይወት ቁሳዊ እውነቶችን ለመቆጣጠር ብቻ ነው፡፡ በመሰረታዊነት ሕይወትህን ፍፁም በሆነ አመክንዮ የምትመለከት ከሆነ ሕይወት ምንም ትርጉም አይኖረውም፤ ስለዚህ ራስህን በአመክንዮ ለመያዝ የምትሞክር ከሆነ ሙሉ በሙሉ ምስቅልቅል ያልክ ትሆናለህ ማለት ነው፡፡ ነገ በማለዳ ከእንቅልፍህ ስትነቃ የፀሐይ መውጣትን፣ መውጣትን፣ በሰማይ ላይ የሚበሩ ወፎችን አትመልከት፤ የምትወደውን ሰው፣ የልጅህን ፊት ወይም በአትክልቱ ውስጥ ያሉትን አበቦች አታስብ፤ ዝም ብለህ በፍፁም አመክንዮ አስብ፡፡
አሁን፣ በትክክል ከአልጋ መውጣት አለብህ ያ ትንሽ ስራ አይደለም። ወደ መጸዳጃ ቤት ትሄዳለህ፣ ጥርሶችህን ትቦርሻለህ፣ ምግብ ትበላለህ፣ ከዚያ አንዳንድ ስራዎችን ትሰራለህ፣ ትበላለህ፣ ትተኛለህ፤ ነገ ጠዋትም ተመሳሳይ ነገር ታደርጋለህ፡፡ ይህን ነገር ለሚቀጥሉት አርባና ሀምሳ አመታት ደጋግመህ ማድረግ አለብህ፡ የሕይወት ተሞክሮህን ሳትመለከት መቶ በመቶ በምክንያታዊነት አስብ፦ በእርግጥ ጠቃሚ ነው? እባክህ የከፍተኛ አመክንዮ ጊዜያት ራስን የማጥፋት ጊዜዎች መሆናቸውን ተመልከት። ስለ ሕይወት መቶ በመቶ ምክንያታዊ በሆነ መንገድ የምታስብ ከሆነ፣ ለመኖር ምንም ምክንያት አይኖርም፤ እኔና አንተ እዚህ የምንኖርበት ምንም ምክንያት የለም፡፡ ነገር ግን በሕይወትህ ውስጥ አንድ የሚያምር ቅጽበት ከተመለከትክ፣ በድንገት ሁሉም ነገር ብሩህ ይሆንና መኖር ትፈልጋለህ፡፡ የሕይወትህ አመክንዮአዊ ገጽታና የሕይወት ተሞክሮህ ስፋት አንዳቸው ከሌላኛቸው ጋር ተቃራኒ ናቸው፡፡
ሕይወትን በተሞክሮ አይን የምትመለከት ከሆነ፣ ለመኖር የሚያበቃ ምክንያት ይኖርሃል፡፡ ሕይወትን በምክንያታዊነት የምትመለከት ከሆነ ደግሞ ለመኖር ምንም ምክንያት አይኖርም፡፡ ሰዎች በበርካታ ምክንያቶች ራሳቸውን ያጠፋሉ፡፡ በአጠቃላይ ግን ሰው ራሱን የሚያጠፋው የነበረውን ተሞክሮ መልሶ ለማየት ፍቃደኛ ባለመሆኑ ነው። ለምሳሌ በጤና ምርመራ ሲወድቅ፣ የትዳር አጋር ጥሎት ሲሄድ ወይም ንብረቱን ሲያጣ ራሱን ሊያጠፋ ይችላል፡፡ ለምሳሌ ዛሬ ባልሽ ወይም ሚስትህ ጥሎሽ ወይም ጥላህ ሄደዋል እንበል፡፡ በምክንያታዊነት የምታስብ ከሆነ፣ “መላ ሕይወቴ ይህንን ሰው መውደድና ከዚህ ሰው ጋር መሆን ነበር፤ አሁን ይህ ሰው ትቶኝ ሄዷል። የምኖርበት ምክንያት ምንድነው?” ብለህ ታስብና ራስህን ታጠፋለህ። ነገር ግን ባልሽ ወይም ሚስትህ ትተው ከሄዱ ምናልባት በሕይወትህ ውስጥ ሙሉ ለሙሉ አዲስ እድል ሊሆን ይችላል፡፡ ነፃ ስለሆንክ ብቻ ከአንድ የሕይወት ገጽታ ምናልባትም ያልገመትካቸው ነገሮች ያጋጥሙህ ይሆናል፡፡
@zephilosophy
@zephilosophy
አእምሮ እና ተመስጦ
ሳድጉሩ
አእምሮህ ተመስጦ አይወድም፡፡ መቀመጥና ማሰላሰል ስትፈልግ አእምሮህ ያንን እንዳታደርግ ሁሉንም ነገር ያደርጋል፡፡ በመጀመሪያ “ነገ ታደርገዋለህ” ይልሃል። “ነገ” የአእምሮ ጥልቅ ማታለያ ነው፡፡ አእምሮህ “አላደርገውም” ካለ፣ ኢጎህ “አደርገዋለሁ” ማለት ተፈጥሮው ነው፡፡ አንተ የሆነ ነገር እንድታደርግ ከፈለግክ ይህን ለማድረግ አንዱ ቀላል መንገድ “እባክህ አታድርገው፡፡ ማድረግ
አይገባህም፣ አታድርገው፡፡” ማለት _ ነው፡፡ ነገር ግን የኢጎ ባህሪይ ስለሆነ ታደርገዋለህ፡፡ ስለዚህ አእምሮ “ነገ እናድርገው ነው እንጂ በፍፁም “አላደርገውም” አይልም፡፡ ነገ ደግሞ በፍጹም አይመጣም፡፡ ሰዎች በሕይወታቸው ውስጥ ሊያደርጓቸው የሚገቡ ብዙ ነገሮችን “ነገ ብለዋል፡፡ ለራሳቸው ደስታ ሳይቀር “ነገ” ይላሉ፡፡
ለተመስጦ ወይም ለማሰላሰል ስትቀመጥ የአእምሮ “ነገ” የሚለው ዘዴ ካልተሳካና “አይ፣ ነገ አይሆንም፤ ዛሬ ለማድረግ ቆርጫለሁ” ካልክ፣ ሁለተኛ ዘዴውን ይሞክራል፡፡ ሳምንቱን ሙሉ ለማስታወስ ስትሞክር የነበረው የስልክ ቁጥር ድንገት ብልጭ ይልልህና ወደ ስልክህ ትሮጣለህ ተመስጦውም ያበቃል፡፡
ይህንንም ከተቋቋምክና ወደ ስልኩ ሳትሮጥ ቁጭ ብለህ ተመስጦህን ከቀጠልክ፣ በሁለት እና ሶስት ደቂቃዎች ውስጥ ግማሽ ደርዘን የሚሆኑ የተለያዩ የሰውነትህ ክፍሎች በድንገት ሊያሳክኩህ ይጀምራሉ፡፡ የተቀመጥከው ተመስጦ ካልሆነ ምንም ነገር አይከሰትም፤ ለማሰላሰል ከሆነ ግን በሁሉም ቦታ ብዙ ነገሮች መከሰት ይጀምራሉ፡፡ ለዚህ ምክንያቱ አእምሮ ሰውነት ከተረጋጋ እርሱም እንደሚረጋጋ ስለሚያውቅ ነው፡፡ አእምሮ ይህ እንዲሆን ከፈቀደ ደግሞ ባርያ እንደሚሆን ያውቃል።
ራስህን ብታስተውል፤ ስትቆም፣ ስትቀመጥና ስትናገር ሰውነትህ ምን ያህል አላስፈላጊ እንቅስቃሴዎችን እንደሚያደርግ ታያለህ። ሕይወትህን ስትመለከት ምናልባት ከግማሽ በላይ ጊዜ የወሰዱት እነዚህ አላስፈላጊ ነገሮች እንደሆኑ ትገነዘባለህ፡፡ በሰውነትህ ውስጥ አንተ ራስህ ግድ የማትሰጣቸው ብዙ አላስፈላጊ ሀሳቦችና እንቅስቃሴዎች አሉ፡፡ ነገር ግን ሰውነት መረጋጋት ከቀጠለ፣ አእምሮም ቀስ በቀስ መርገብ ይጀምራል፡፡
አእምሮ የመጨረሻ ዘዴውን የሚጠቀመውም በዚህ ጊዜ ነው፡፡ “ምን አገኛለሁ? ከዚህ ተመስጦ የምወስደው ምንድን ነው?” የሚል ጥያቄ ይጠይቃል፡፡ በአእምሮ ውስጥ ለሚከናወኑ ተግባራት ሁሉ ቁልፍ የሆነው ይሀ ጥያቄ ነው፡፡ የአእምሮ ጥያቄ ሁሉ “ምን ማግኘት እችላለሁ?” ብቻ ነው፡፡ ይህንን ስሌት ችላ ብለህ ካለፍክ ዘጠና በመቶ የሆነው መንፈሳዊ ስራ አልቋል ማለት ነው፡፡ ቀሪው አስር በመቶ፣ በራሱ የሚከሰት ነው፡፡ ከዚህ ምንም መጠቀም የለብህም። ስለዚህ በየቀኑ ተመስጦ በማድረግ የተወሰነ ጊዜ ማባከን ብቻ ተማር፡፡
በተመስጦ ውስጥ እያለህ ምንም ነገር መከሰት አያስፈልገውም። በተመስጦ ውስጥ ሆነህ አንድ የምታስታውሰው ነጥብ ከፈለግክ፣ ጥቃቅን ነገሮችን ብቻ ትወስዳለህ፡፡ እውነተኛው ነገር ግን ወደ አንተ ሊመጣ አይችልም፡፡ እውነተኛውን ነገር የምትፈልግ ከሆነ ደግሞ ይህንን በተመስጦ ውስጥ ምንም ነገር እንዳይከሰት የማድረግ ቀላል ስሌትን ብቻ መፈፀም አለብህ፡፡ ይህንን ከዚህ ምን አገኛለሁ? የሚለውን የአእምሮ ስሌት መተው ከቻልክ፣ አእምሮ የሚያደርገውን የማያቋርጥ ሩጫ ገታህ ማለት ነው፡፡ እናም አእምሮ በድንገት የተለየና ድንቅ ባሪያ ይሆናል፡፡
አሁን አእምሮህ አለቃ፣ አንተ ደግሞ ባሪያ ነህ፡፡ የተመስጦ ዋናውን ገጽታ የበለጠ እያሰላሰልክ ስትሄድ፤ አንተ አለቃ፣ አእምሮህ ደግሞ ባሪያ ይሆናል፤ ሁልጊዜም መሆን ያለበት እንደዚህ ነው። አእምሮ ማለቂያ በሌለው መከራ ውስጥ የሚያሳልፍህ አስፈሪ ጌታ ቢሆንም፣ በተወሰነ መንገድ ከያዝከው ግን የምትፈልገውን ማንኛውንም ነገር ልታደርግበት የምትችል ድንቅ ባሪያ ነው፡፡
@zephilosophy
@zephilosophy
Владелец канала не предоставил расширенную статистику, но Вы можете сделать ему запрос на ее получение.
Также Вы можете воспользоваться расширенным поиском и отфильтровать результаты по каналам, которые предоставили расширенную статистику.
Также Вы можете воспользоваться расширенным поиском и отфильтровать результаты по каналам, которые предоставили расширенную статистику.
Подтвердите, что вы не робот
Вы выполнили несколько запросов, и прежде чем продолжить, мы ходим убелиться в том, что они не автоматизированные.
Наш сайт использует cookie-файлы, чтобы сделать сервисы быстрее и удобнее.
Продолжая им пользоваться, вы принимаете условия
Пользовательского соглашения
и соглашаетесь со сбором cookie-файлов.
Подробности про обработку данных — в нашей
Политике обработки персональных данных.