This is Ministry of Education's Official Telegram Channel.
For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe
Информация о канале обновлена 18.08.2025.
This is Ministry of Education's Official Telegram Channel.
For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe
ማሳሰቢያ
በ2017 የትምህርት ዘመን 8ኛ ክፍልን አጠናቃችሁ ወደ 9ኛ ክፍል የተዛወራችሁና መስፈርቱን በማሟላት ትምህርት ሚኒስቴር ባስገነባቸው ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተመዝግባችሁ ለመማር ፍላጎት ያላችሁ ተማሪዎች በ https://sbs.moe.gov.et ላይ በመግባት ማመልከት የምትችሉ ሲሆን፣ በ2015 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ሚኒስትሪ በክልላችሁ ያልተጀመረባችሁ አካባቢዎች የ6ኛ ክፍል ውጤታችሁን ከፊትም ከጀርባም ስካን አድርጋችሁ እንዲሁም ስምንተኛ ክፍል ሚኒስትሪ ያልደረሰላችሁ ተማሪዎች ደግሞ የኦን ላይን ውጤታችሁን ስካን አድርጋችሁ ማያያዝ የመትችሉ መሆኑን እየገለጽን፣
በእነዚህ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ተቀጥራችሁ ለማስተማር ፍላጎቱ ያላችሁ መምህራን ደግሞ በ https://sbs.moe.gov.et/carrier/teacher ላይ በመግባት ማመለከት የምትችሉ መሆኑን በድጋሚ ለመግለጽ እንወዳለን ።
ትምህርት ሚኒስቴር
ማስታወቂያ
ትምህርት ሚኒስቴር ባስገነባቸው ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች በ2017 የትምህርት ዘመን 8ኛ ክፍልን ካጠናቀቁ ተማሪዎች መካከል አወዳድሮ ማስተማር ይፈልጋል። በመሆኑም መስፈርቱን የምታሟሉ ተማሪዎች ከነሐሴ 05/2017 እስከ ነሐሴ 15/2017 ድረስ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ለመመዝገን ይህንን ሊንክ መጠቀም ትችላላችሁ።
https://sbs.moe.gov.et/apply
በህጻናት ተማሪዎች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶች በበርካታ የሀገራችን አካባቢዎች ሥር እየሰደዱ መምጣታቸው አሳሳቢ መሆኑ ተገለጻ።
========================
(ነሃሴ 2/2017 ዓ.ም) በህጻናት ተማሪዎች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶች ለመከላከል ከመላ ሀገሪቱ ከተውጣቱ የተማሪ ወላጅ ህብረት አመራሮችና አባላት ጋር የግንዛቤ ማስጨበጫ አውደጥናት ተካሂዷል።
በአውደ ጥናቱ መከፈቻ የተገኙት በትምህርት ሚኒስቴር የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ምህረተክርስቶስ ታምሩ ባስተላለፉት መልዕክት በሀገራችን የኤችኣይቪ ሥርጭት፣ያልታቀደ እርግዝና፣ጾታን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶችና የህጻናት ጋብቻ ችግሮች በበርካታ አካባቢዎች ሥር እየሰደዱ መምጣቸው ጥናቶች እንደሚያመላክቱ ገልጸው ይህም አሳሳቢ መሆኑን ተናግረዋል።
አክለውም ተሳታፊዎች ከዚህ ስልጠና እንደተመለሱ ወደ ስራ ለመግባት የድርጊት መርሃ-ግብር ማዘጋጀታቸውን ጠቅሰው በዚህም ማህበረሰቡ ለልጆቹ ደህንነትና ትምህርት ትኩረት በመስጠት የድርሻውን እንዲወጣ ቀጣይነት ያለው ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራ መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤https://www.facebook.com/share/p/1B45SQpyi1/
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከሁሉም ክልሎች የሚመጡ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎችን እንደ አንድ የሀገር ልጆች የሚቀበልበት የጎንደር ቃል ኪዳን ቤተሰብ ፕሮግራም ለጎንደር ብቻ ሳይሆን ለሀገሩም ምሳሌ የሚሆን መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ገለፁ፤
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ 70ኛ እና ማስተማሪያ ሆስፒታሉ 100ኛ ዓመት ምሥረታ በዓል የማጠናቀቂያ መርሃ ግብር ተካሂዷ።
-------------------------------------------------------
(ሐምሌ 30/2017 ዓ.ም) በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ይህ ክብረ በዓል የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ለጎንደርና ለአካባቢው ህዝብ ያለውን ፋይዳ እንዲሁም ህዝቡ ለተቋሙ ያለውን አክብሮት ያየንበት ነው ብለዋል።
በዓሉ ከዩኒቨርሲቲውና ከሆስፒታሉ ምስረታ በላይ በተለይ በዚህ አስቸጋሪ ጊዜ የጎንደርን ህዝብ ጥልቅ የሆነ የኢትዮጵያዊነት ስሜት ያንፀባረቀበትም እንደነበር አንስተዋል።
በተለይም የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከሁሉም ክልሎች የሚመጡ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎችን እንደ አንድ የሀገር ልጆች የሚቀበልበት “የጎንደር ቃል ኪዳን ቤተሰብ ፕሮግራም” ለጎንደር ብቻ ሳይሆን ለሀገራችንም ምሳሌ የሚሆን ነው ብለዋል።
ዩኒቨርስቲዎች አንዱ እንዲያደርጉ የምንፈልገው የመንደር ሳይሆኑ የሀገር ሀብት እንዲሆኑ ነው ያሉት ሚኒስትሩ ፤
በተለይ አሁን ዋና ሪፎርም ዩኒቨርሲቲዎች ራሳቸውን እንዲችሉ በነፃነት የሚሰሩ፣ በነፃነት የሚያስቡ እውነትንና እውቀትን የሚፈልጉ ሰዎች የተሰባሰቡባቸው ሰላማዊ ቦታ እንዲሆኑ መሆኑን አብራርተዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤
https://www.facebook.com/share/p/1D3gaudqWn/
የአካቶ ትምህርት ማዕከላትን በማስፋትና በማጎልበት ረገድ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑ ተመላከተ።
--------------------------------------------
(ሀምሌ 30/ 2017 ዓ.ም) የአካቶ ትምህርት በስፋትና በትኩረት የሚተገበር ጉዳይ መሆኑን በአዲሱ የትምህርት ፓሊሲ ላይ ተመላክቷል።
በፓሊሲው የተቀመጠውን የአካቶ ትምህርት ትግበራ ከግብ ለማድረስ በትምህርት ሚኒስቴር በኩል በመከናወን ላይ ያሉ ጅምር ስራዎች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን በትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ፕሮግራሞችና ጥራት መሻሻል መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ዩሀንስ ወጋሶ ገልጸዋል ።
ትግበራውን ወደተሻለ ደረጃ ከፍ ለማድረግ የተባባሪና አጋር ድርጅቶች ሚና ከፍተኛ አስተዋጾ እያደረጉ መሆኑን መሪ ስራ አስፈጻሚው አያይዘው ተናግረዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር ከፊንላንድ መንግስት ጋር በመተባበር "አካታችና ጥራት ያለው የመምህራን ስልጠና" (Teacher Education for Inclusion and Quality (TEFIQ) ፕሮጀክት ትግበራ የመምህራን ትምህርት ኮሌጆች አሰልጣኝ መምህራን አቅም ለማጎልበትና የአካቶ ትምህርት ትግበራ ማዕከላትን ለማስፋትና ለማጎልበት በሚከናወኑ ተግባራት ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን አመላክተዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤
https://www.facebook.com/share/p/1QtomLxryH/
በአገሪቱ በተመረጡ 30 ዩኒቨርስቲዎች የሚሰጠው የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ስልጠና መሰጠት ጀመረ።
በስልጠናው ከ84 ሺ የሚበልጡ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ይሳተፋሉ፡፡
-------------------------------------------
(ሐምሌ 28/2017 ዓ.ም) ስልጠናውን መስጠት ከጀመሩ ዩኒቨርስቲዎች አንዱ የሆነው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የትምህርትና ቋንቋዎች ጥናት ኮሌጅ ኤክስኪዩቲቭ ዲን የቆየዓለም ደሴ (ዶ/ር) ዩኒቨርስቲው ተማሪዎችን በጥሩ ሁኔታ ለማሰልጠን የአሰልጣኝ መምህራን ፣ የስልጠና ክፍሎች፣ የተማሪዎች ማደሪያ ፣ የካፍቴሪያ እና የማሰልጠኛ ሞጁልና ምዝገባ አጠናቆ ስልጠና መጀመሩን ተናግረዋል፡፡
ስልጠናው መምህራን በሚያስተምሩበት ትምህርት ዓይነት ፣ በማስተማር ስነ ዘዴ፣ በቴክኖሎጂ አጠቃቀም እንዲሁም በስነ ልቦናዊ ፣ ማህበራዊና የጤና ጉዳዮችን አካቶ የያዘና ሰፊ ክፍተትን የሚሞላ በመሆኑ ሰልጣኞች ተረጋግተው መሰልጠንና የመጡበትን አላማ ሳይረሱ ክፍል ውስጥም ሆነ ከሌሎች ጓደኞቻቸውና ከአሰልጣኝ መምህራን ጋር መነጋገር እና መማር እንዳለባቸው ጠቁመዋል፡፡ ሙሉ መረጃውን ይህንን ሊንክ በመጫን ማግኘት ይችላሉ፤
https://www.facebook.com/share/p/1B56YnWyGA/
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የለውጥ ምክር ቤት ዓመታዊ ጉባዔ መካሄድ ጀመረ።
የኢትዮጵያ የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የለውጥ ምክር ቤት ጉባኤ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ አስተናጋጅነት "የከፍተኛ ትምህርት ለላቀ ተፅዕኖ" በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ይገኛል።
-----------------------------------------------------
(ሐምሌ 28/2017 ዓ.ም) በመርሃ ግብሩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሽኔ ይህ ጉባኤ በትምህርት ዘርፍ እየተተገበሩ ያሉ የሪፎርም ተግባራት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምን ያህል ለውጥ ተመዘገበ ተብሎ የሚገመገምበትና የወደፊት አቅጣጫ የሚቀመጥበት መሆኑን ገልፀዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተወዳዳሪ፣ የበለፀገች፣ ሉዓላዊት፣ ዴሞክራሲያዊት እና ፍትሃዊ የሆነች ኢትዮጵያን ለመፍጠር ሚናቸው የጎላ መሆኑንም አንስተዋል።
በዚህም "የትምህርት ጥራት የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በገቡት የቁልፍ ተግባራት መለኪያ ውል መሠረት ጥራትን ለማረጋገጥ በተሰሩና ባልተሰሩ ስራዎች ዙሪያ ለመመካከር እድል ይፈጥራል ብለዋል።
በተጨማሪም መድረኩ በዩኒቨርሲቲዎች መካከል ልምድ ለመለዋወጥ የሚያስችል መሆኑንም ተናግረዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤
https://www.facebook.com/share/p/1HqM5HKsed/
Владелец канала не предоставил расширенную статистику, но Вы можете сделать ему запрос на ее получение.
Также Вы можете воспользоваться расширенным поиском и отфильтровать результаты по каналам, которые предоставили расширенную статистику.
Также Вы можете воспользоваться расширенным поиском и отфильтровать результаты по каналам, которые предоставили расширенную статистику.
Подтвердите, что вы не робот