This is Ministry of Education's Official Telegram Channel.
For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe
Информация о канале обновлена 21.11.2025.
This is Ministry of Education's Official Telegram Channel.
For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe
በቴክኖሎጂ የተደገፈ አሠራር ሥርዓትን በመዘርጋት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ሥራ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ።
ህዳር 10/2018 ዓ.ም ትምህርት ሚኒስቴር ) በበይነ መረብ የተደገፈ የአውቶሜሽን አገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓትን ወደ ተግባር ለማስገባት የሚያስችል ስልጠና ለባለሙያዎች ተሰጥቷል።
የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት በቴክኖሎጂ የተደገፈ ዘመናዊ አሠራር ሥርዓትን በመዘርጋት ለተገልጋዮች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል፡
በቴክኖሎጂ የዘመነ አሰራር ጊዜን፣ ጉልበትን፣ ገንዘብንና ሌሎች ወጪዎችን በመቀነስ አገልግሎቶችን ጥራት ባለው ሁኔታ ተገልጋዮች ባሉበት ቦታ በተመሳሳይ ጊዜ ተደራሽ ለማድረግ እድል የሚፈጥር በመሆኑ እነዚህን አገልግሎትዮች ዲጅታላይዝ ማድረግ ዋነኛ ዓላማ መሆኑን ዶ/ር ኤባ ተናግረዋል፡፡ ሙሉ ዜናውን https://web.facebook.com/share/p/17eVUr1GXr/
ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡-
በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
ዩቱዩብ- https://www.youtube.com/@ministry-of-education-ethiopia
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/.../ministry-of-education-ethiopia
በዌብሳይት - www.moe.gov.et ይከታተሉ
በትምህርት ቤቶች የጓሮ እርሻ ሥራን ከመደበኛ ትምህርት ጋር በማቀናጀት ተማሪዎች ጽንሰ ሀሳቦችን እንዲተገብሩና የህይወት ክህሎቶችን እንዲያዳብሩ እየተሰራ መሆኑ ተጠቆመ
(ሕዳር 08/2018 ዓ.ም) ለተመረጡ የትምህርት ቤት ርዕሳነ መምህራንና የግብርና ባለሙያዎች በትምህርት ቤቶች የጓሮ እርሻ ልማት ላይ ያተኮረ ስልጠናና ትምህርታዊ ጉብኝት ተደርጓል።
የትምህርት ፕሮግራሞቾና ጥራት መሻሻል መሪ ስራ አስፈጻሚ ዩሐንስ ወጋሶ (ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት በትምህርት ቤቶች የጓሮ እርሻ ሥራን በማስፋፋት ተማሪዎች የህይወት ክህሎቶችን እንዲያዳብሩ እየተሰራ ነው።
በትምህርት ቤቶች የጓሮ እርሻዎች መስፋፋት አመጋገብና ሥነ ምግብን በማሻሻል፣ የምገባ ወጪን በመቀነስ፣ በአካባቢ ጥበቃ፣ በሥራ እድል ፈጠራና በሌሎችም ትምህርት ቤቶችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ዶ/ር ዩሐንስ ተናግረዋል።
ትምህርት ቤቶች የመማማሪያና የማህበረሰብ ሽግግር የሚደረግባቸው ማዕከላት በመሆናቸው ምርታማነታቸው በማሳደግ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተሰራ መሆኑንም መሪ ስራ አስፈጻሚው ገልጸዋል።
ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡-
በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
ዩቱዩብ- https://www.youtube.com/@ministry-of-education-ethiopia
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/.../ministry-of-education-ethiopia
በዌብሳይት - www.moe.gov.et ይከታተሉ
የክብር ዶክትሬት የተሠጣቸውን ግለሰቦች በመጠሪያነት መጠቀም የማይቻል መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ገለፁ።
--------------------------- // ----------------------------
(ሕዳር 05/2017 ዓ.ም) በዛሬው እለት የህዝብ ተወካዮች የሰው ሃብት ልማት ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የትምህርት ዘርፉን የ1ኛ ሩብ ዓመት ሥራ አፈፃፀም ተመልክቷል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በከፍተኛ ትምህር ተቋማት የክብር ዶክትሬት አሰጣጥን በተመለከተ ችግር የነበረበት በመሆኑ ወጥ አሰራር መከተል በማስፈለጉ የክብር ዶክትሬት አሰጣጥን ሀገራዊ መመሪያ ተዘጋጅቶ ለትግበራ ዝግጁ መሆኑን ገልፀዋል።
ሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም በመመሪያው መሰረት ተፈፃሚ ማድረግ ያለባቸው ሲሆን የክብር ዶክትሬት ማዕረግ የሚያገኙ ሰዎች ዶክተር ወይንም የክብር ዶክተር በሚል መጠሪያነት መጠቀም እንደማይቻል አሳስበዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤
https://www.facebook.com/share/p/17ogQjrnLd/
አመታዊ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ሥራዎች አውደ ርዕይና ውድድር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተገለጸ፤
------------------------------- // ------------------------------
(ህዳር 04/ 2018 ዓ.ም) በትምህርት ሚኒስቴር እና ተባባሪ አካላት አዘጋጅነት በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ አስተናጋጅነት ሲካሄድ የነበረው 10ኛው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ሥራዎች አውደ ርዕይና ውድድር ተጠናቋል።
በመርሃ-ግብሩ ማጠቃለያ ላይ የተገኙት የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ መርሃ-ግብሩ ተማሪዎችና መምህራን የፈጠራ ሀሳባቸውን ለሌሎች አካፍለው ድጋፍና ግብዓት በማሰባሰብ ወደ ውጤታማ ምርትና አገልግሎት ለመቀየር የሚጥሩበት አውድ በመሆኑ በሚመለከታቸው የባለድርሻ አካላት ርብርብ ተጠናክሮ መቀጠል የሚገባው መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በሀገራት መካከል ለተፈጠረው የዕድገት ልዩነት መሰረታዊውና ዋነኛው ምክንያት ለቴክኖሎጂና ፈጠራ ስራዎች የተሰጠው ትኩረትና በዚህ ረገድ የተሰሩ ሥራዎች መሆናቸውን አንስተዋል፡፡
ሚኒስትር ዴታው አክለውም በአካባቢያቸው ያሉ የቴክኖሎጂና ፈጠራ ሥራ ዝንባሌና ተሰጣኦ ያላቸው ተማሪዎችን የመደገፍና የማብቃት ሥራ ለዩኒቨርሲቲዎች ከተሰጡት ቁልፍ ተግባራት መካከል አንዱ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፣
https://www.facebook.com/share/p/16VyKcrspR/
ማስታወቂያ
ለትምህርት ማህበረሰቡና ባለድርሻ አካላት በሙሉ፤ በረቂቅ መመሪያዎች ላይ አስተያየት እንድትሰጡ ስለመጠየቅ፤
የትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ፕሮግራሞችና ጥራት መሻሻል መሪ ስራ አስፈጻሚ በ3 የተለያዩ ጉዳዮች ማለትም፤
1. ትምህርትን በአደጋ ጊዜ ለማስቀጠልየተዘጋጀ መመሪያ (የመጀመሪያ ረቂቅ) ሊንክ = https://forms.gle/DxVRi8nBuu6HBD7F7
2. የገጠር እና ጠረፋማ አካባቢዎችየትምህርት ድጋፍ አተገባበር መመሪያ (የመጀመሪያ ረቂቅ) ሊንክ = https://forms.gle/uH1tvfKmGrWEwhah6
3. ነፃና የግዴታ ትምህርት አተገባበር መመሪያ (የመጀመሪያ ረቂቅ) ሊንክ= https://forms.gle/F2RHcXKdUUmrCvik6 አዘጋጅቷል።
በመሆኑም ሰነዶቹን በማንበብ አስተያየት እንድትሰጡ እየጠየቅን፤
ለመጀመር ከእያንዳንዱ ረቂቅ መመሪያ ፊት ለፊት ያሉትን ሊንኮች መጫን፤
በመቀጠል ማስፈንጠሪያ የሚለውን በመጫን ሰነዱን ማግኘት ትችላላችሁ፣
ሰነዱን ካነበባችሁ በኋላ የተጠየቁ መረጃዎችንና አስተያየታችሁን ሞልታችሁ (submit) የሚለውን በመጫን መረጃውን መላክ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
ትምህርት ሚኒስቴር
በኢትዮጵያ እና እስራኤል መካከል ያለውን የትምህርትና ስልጠና ትብብር ማጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ።
------------------ // ------------------
(ሕዳር 04/2018 ትምህርት ሚኒስቴር) የትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር የሆኑትን ዶ/ር አብርሃም ንጉሴ ጋር ተወያይተዋል።
በዚሁ ጊዜ ሁለቱ ወገኖች በነበራቸው ውይይት ወጣቶችን ተጠቃሚ በሚያደርጉ የትምህርትና ስልጠና ጉዳዮች ዙሪያ አብሮ የመስራት ፍላጎት ያላቸው መሆኑን ገልጸዋል።
ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በተለይም የመምህራንና የተማሪዎች አቅምን መገንባት በሚያስችሉ ፕሮጀክቶች ላይ ከእስራኤል መንግስትና ተቋማት ጋር አብሮ ለመስራት ፍላጎት ያለ መሆኑን ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አብርሃም ንጉሴ(ዶ/ር) በበኩላቸው በኢትዮጵያና በእስራኤል መንግስታትና ህዝብ መካከል ለረጅም ጊዜ የቆየ ወዳጅነት መኖሩን አንስተው ይህንን አጠናክሮ በመቀጠል በሁለቱ ሀገራት መካከል በትምህርትና ስልጠና ዘርፍ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ያለውን ትብብር ማጠናከር እንደሚገባ አንስተዋል።
በውይይቱ ላይ ዩኒስትሪም (Unistream) የተባለ የእስራኤል ድርጅት ወጣቶችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የትምህርትና ስልጠና ስራዎች ላይ በትብብር ለመስራት ፍላጎት ያለው መሆኑም ተጠቅሷል።
ማስታወቂያ
ለትምህርት ማህበረሰቡና ባለድርሻ አካላት በሙሉ፤ በረቂቅ መመሪያዎችና ደንብ ላይ አስተያየት እንድትሰጡ ስለመጠየቅ፤
የትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ፕሮግራሞችና ጥራት መሻሻል መሪ ስራ አስፈጻሚ በ3 የተለያዩ ጉዳዮች ማለትም፤
1. የአጠቃላይ ትምህርት ተቋማት አመራር፣ አደረጃጀት የህብረተሰብ ተሳትፎና የፋይናንስ ረቂቅ መመሪያ፣( ሊንክ = https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLScdrHGMOV3gb_aOhiFZsxGU1JAB178bvAiDRufSIPFTIfrj_g/viewform)
2. በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥታዊ ያልሆኑ የትምህርት ተቋማት ረቂቅ ደንብ ፤ ( ሊንክ = https://forms.gle/LpwGdAu7mBYRUNNU6)
3. የአጠቃላይ ትምህርት የውስጥ ኢንስፔክሽን እና ሱፐርቪዥን አተገባበር ረቂቅ መመሪያ (ሊንክ = https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSdoOaNWgbbPX8M2dEpqcBFOlLBefpFtzeKYyu1HOxEiycCjg/viewform?usp=sharing&ouid=111388231034755887607) አዘጋጅቷል።
በመሆኑም ሰነዶቹን በማንበብ አስተያየት እንድትሰጡ እየጠየቅን፤
ለመጀመር ከእያንዳንዱ ረቂው መመሪያ ፊት ለፊት ያሉትን ሊንኮች በመጫን፤
በመቀጠል ማስፈንጠሪያ የሚለውን በመጫን ሰነዱን ማግኘት ትችላላችሁ፣
ሰነዱን ካነበባችሁ በኋላ የተጠየቁ መረጃዎችንና አስተያየታችሁን ሞልታችሁ (submit) የሚለውን በመጫን መረጃውን መላክ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
ትምህርት ሚኒስቴር
ማስታወቂያ፤
በፌዴራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በመምህርነት ለመወዳደር የተመዘገባችሁና እና ለቃለ መጠይቅ የተመረጣችሁ ተወዳዳሪዎች በሙሉ፤
ቃለ መጠይቁ የሚደረገው እሁድ ሕዳር 07/2018 ዓ.ም ሲሆን በተጠቀሰው ቀን ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርስቲ እንድትገኙ እያሳወቅን ስትመጡ፤
ሙሉ የትምህርት ማስረጃ ኦርጂናል እና ኮፒ፣
ልዩ የክረምት የአቅም ግንባታ ስልጠና እና የአንድ አመት ልዩ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህርነት ስልጠና ሰርትፍኬት፣
የሙያ ፍቃድ እና እድሳት ሰርትፍኬት፣
በመምህርነት ተገቢነት ያለው የስራ ልምድ ማስረጃ የሚገልጽ ደብዳቤ መያዝ የሚያስፈልግ መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን።
ለቃለ መጠይቅ የተመረጣችሁ መምህራን ስም ዝርዝር ከዚህ ማስታወቂያ ጋር ተያይዟል ፡፡
Владелец канала не предоставил расширенную статистику, но Вы можете сделать ему запрос на ее получение.
Также Вы можете воспользоваться расширенным поиском и отфильтровать результаты по каналам, которые предоставили расширенную статистику.
Также Вы можете воспользоваться расширенным поиском и отфильтровать результаты по каналам, которые предоставили расширенную статистику.
Подтвердите, что вы не робот
Вы выполнили несколько запросов, и прежде чем продолжить, мы ходим убелиться в том, что они не автоматизированные.
Наш сайт использует cookie-файлы, чтобы сделать сервисы быстрее и удобнее.
Продолжая им пользоваться, вы принимаете условия
Пользовательского соглашения
и соглашаетесь со сбором cookie-файлов.
Подробности про обработку данных — в нашей
Политике обработки персональных данных.