This is Ministry of Education's Official Telegram Channel.
For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe
Информация о канале обновлена 18.11.2025.
This is Ministry of Education's Official Telegram Channel.
For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe
የክብር ዶክትሬት የተሠጣቸውን ግለሰቦች በመጠሪያነት መጠቀም የማይቻል መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ገለፁ።
--------------------------- // ----------------------------
(ሕዳር 05/2017 ዓ.ም) በዛሬው እለት የህዝብ ተወካዮች የሰው ሃብት ልማት ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የትምህርት ዘርፉን የ1ኛ ሩብ ዓመት ሥራ አፈፃፀም ተመልክቷል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በከፍተኛ ትምህር ተቋማት የክብር ዶክትሬት አሰጣጥን በተመለከተ ችግር የነበረበት በመሆኑ ወጥ አሰራር መከተል በማስፈለጉ የክብር ዶክትሬት አሰጣጥን ሀገራዊ መመሪያ ተዘጋጅቶ ለትግበራ ዝግጁ መሆኑን ገልፀዋል።
ሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም በመመሪያው መሰረት ተፈፃሚ ማድረግ ያለባቸው ሲሆን የክብር ዶክትሬት ማዕረግ የሚያገኙ ሰዎች ዶክተር ወይንም የክብር ዶክተር በሚል መጠሪያነት መጠቀም እንደማይቻል አሳስበዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤
https://www.facebook.com/share/p/17ogQjrnLd/
ማስታወቂያ
ለትምህርት ማህበረሰቡና ባለድርሻ አካላት በሙሉ፤ በረቂቅ መመሪያዎችና ደንብ ላይ አስተያየት እንድትሰጡ ስለመጠየቅ፤
የትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ፕሮግራሞችና ጥራት መሻሻል መሪ ስራ አስፈጻሚ በ3 የተለያዩ ጉዳዮች ማለትም፤
1. የአጠቃላይ ትምህርት ተቋማት አመራር፣ አደረጃጀት የህብረተሰብ ተሳትፎና የፋይናንስ ረቂቅ መመሪያ፣( ሊንክ = https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLScdrHGMOV3gb_aOhiFZsxGU1JAB178bvAiDRufSIPFTIfrj_g/viewform)
2. በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥታዊ ያልሆኑ የትምህርት ተቋማት ረቂቅ ደንብ ፤ ( ሊንክ = https://forms.gle/LpwGdAu7mBYRUNNU6)
3. የአጠቃላይ ትምህርት የውስጥ ኢንስፔክሽን እና ሱፐርቪዥን አተገባበር ረቂቅ መመሪያ (ሊንክ = https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSdoOaNWgbbPX8M2dEpqcBFOlLBefpFtzeKYyu1HOxEiycCjg/viewform?usp=sharing&ouid=111388231034755887607) አዘጋጅቷል።
በመሆኑም ሰነዶቹን በማንበብ አስተያየት እንድትሰጡ እየጠየቅን፤
ለመጀመር ከእያንዳንዱ ረቂው መመሪያ ፊት ለፊት ያሉትን ሊንኮች በመጫን፤
በመቀጠል ማስፈንጠሪያ የሚለውን በመጫን ሰነዱን ማግኘት ትችላላችሁ፣
ሰነዱን ካነበባችሁ በኋላ የተጠየቁ መረጃዎችንና አስተያየታችሁን ሞልታችሁ (submit) የሚለውን በመጫን መረጃውን መላክ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
ትምህርት ሚኒስቴር
ማስታወቂያ፤
በፌዴራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በመምህርነት ለመወዳደር የተመዘገባችሁና እና ለቃለ መጠይቅ የተመረጣችሁ ተወዳዳሪዎች በሙሉ፤
ቃለ መጠይቁ የሚደረገው እሁድ ሕዳር 07/2018 ዓ.ም ሲሆን በተጠቀሰው ቀን ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርስቲ እንድትገኙ እያሳወቅን ስትመጡ፤
ሙሉ የትምህርት ማስረጃ ኦርጂናል እና ኮፒ፣
ልዩ የክረምት የአቅም ግንባታ ስልጠና እና የአንድ አመት ልዩ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህርነት ስልጠና ሰርትፍኬት፣
የሙያ ፍቃድ እና እድሳት ሰርትፍኬት፣
በመምህርነት ተገቢነት ያለው የስራ ልምድ ማስረጃ የሚገልጽ ደብዳቤ መያዝ የሚያስፈልግ መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን።
ለቃለ መጠይቅ የተመረጣችሁ መምህራን ስም ዝርዝር ከዚህ ማስታወቂያ ጋር ተያይዟል ፡፡
የትምህርት ስርዓቱን ከዓለም የአየር ንብረት ፣ የቴክኖሎጂ፣ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ለውጥ ጋር በሚጣጣም መልኩ መቃኘት እንደሚገባ ተመላከተ።
34ኛው ሀገር አቀፍ የትምህርት ጉባኤ ባለ 12 ነጥብ አቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቋል።
--------------------------- // -----------------------
(ሕዳር 02/2018 ዓ.ም) የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በጉባኤው ማጠቃለያ ላይ እንደገለጹት የትምህርቱን ሥራ ከአየር ንብረት ፣ ቴክኖሎጂና ከዓለም የፖለቲካና የኢኮኖሚ ለውጥ ጋር በሚጣጣም መልኩ መቃኘትና መተግበር እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ይህ ጊዜ ለውጦችን በመቋቋም ወደ እድል የሚቀይሩ ፣ አገራቸውን የሚወዱና ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግሩ ዜጎችን ለማፍራት በትጋት የምንሰራበት ወቅት መሆኑንም ፕሮፌሰር ብርሃኑ ተናግረዋል።
በመሆኑም በየደረጃው ያሉ መምምህራን በሚያስተምሩበት ትምህርት አይነት የበቁ ሆነው በመገኘት ሙያቸውን ሊያሳድጉና ሊያስከብሩ እንደሚገባ ሚኒስትሩ አሳስበዋል።
በተጨማሪም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለተቋቋሙበት አላማ ቅድሚያ በመስጠት ሃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባም የትምህርት ሚኒስትሩ ተናግረዋል።
የአካል ጉዳተኞችን የመማር ማስተማር ከባቢ ምቹ ለማድረግ አገሪቱ ባላት አቅም ድጋፍ እንደሚደረግም አመልክተዋል።
በበኦሮሚያ ክልል አዳማ ከተማ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፍትሃዊና “ጥራት ያለው ትምህርት ለሁሉም” በሚል መሪቃል የተካሄደው 34ኛው የትምህርት ጉባኤ ባለ 12 ነጥብ አቋም መግለጫ በማውጣትም ተጠናቋል።
የት/ቤት ምገባን በማጠናከር የተማሪዎችን የትምህርት ውጤት ማሳደግ ይገባል፤ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይዎት
--------------------- // ------------------
(ሕዳር 02/2018 ዓ.ም) በ34ኛው የትምህርት ጉባኤ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የትምህርት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፕ/ር ክንደያ ገ/ህይዎት የት/ቤት ምገባን በማጠናከር የተማሪዎችን የትምህርት ውጤት ማሳደግ ይገባል ብለዋል።
ፕ/ር ክንደያ አክለውም የትምህርት ማህበረሰቡ በ “ትምህርት ለትውልድ“ያሳየውን የላቀ ተሳትፎ በአዳሪ እና በሞዴል ት/ቤቶች ግንባታም አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።
የሪፎርም ስራዎቻችንና አበይት ስራዎቻችንን በሚገባ ለይተን በዚህ የትምህርት ዘመን ውጤት ሊያመጡ በሚችል መልኩ መተግባር እንደሚገባም ተናገረዋል።
በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ለታቀዱ የሪፎርም ተግባራት መሳካት ሁሉም አካላት የሚጠበቅባቸውን መወጣት እንዳለባቸው ተገለጸ፤
------------------------ // -----------------------
(ሕዳር 02/2018 ዓ.ም) የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በ34ኛው የትምህርት ጉባኤ ላይ እንደገለጹት በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ለታቀዱ የሪፎርም ተግባራት መሳካት ሁሉም አካላት የሚጠበቅባቸውን መወጣት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
በዚህም የኢንዱስትሪዎችና የትምህርት ተቋማት ትብብር መሥራት ሁለቱንም አካላት የሚጠቅም ተግባር መሆኑን አስገንዝበዋል።
አያይዘውም የዩኒቨርስቲዎች በመማር ማስተማር እና በማህበረሰብ አገልግሎት ስራ ላይ ማተኮር እንዳለባቸው ገልጸው ከየዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን ምገባ ጋር በተያያዘ ኃላፊነት ወስዶ የሚከታተል ተቋም ለማቋቋም እቅድ መኖሩንም ተናግረዋል።
ሚኒስትር ዴኤታው አክለውም የዩኒቨርስቲዎች የትኩረት መስክ ልየታ በሂደት እየተሳካ የሚሄድ መሆኑን ገልጸው በዚህ ሂደት የሚፈጠሩ የመምህራንን እጥረትና ከምችት ለማሰተካከል አዘዋውሮ የማሰራት አቅጣጫ መኖሩንም ጠቁመዋል።
የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን በትኩረት ለመደገፍ የተለየ የህግ ማዕቀፍ እየተዘጋጀ መሆኑንም ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ጨምረው አብራርተዋል።
Владелец канала не предоставил расширенную статистику, но Вы можете сделать ему запрос на ее получение.
Также Вы можете воспользоваться расширенным поиском и отфильтровать результаты по каналам, которые предоставили расширенную статистику.
Также Вы можете воспользоваться расширенным поиском и отфильтровать результаты по каналам, которые предоставили расширенную статистику.
Подтвердите, что вы не робот
Вы выполнили несколько запросов, и прежде чем продолжить, мы ходим убелиться в том, что они не автоматизированные.
Наш сайт использует cookie-файлы, чтобы сделать сервисы быстрее и удобнее.
Продолжая им пользоваться, вы принимаете условия
Пользовательского соглашения
и соглашаетесь со сбором cookie-файлов.
Подробности про обработку данных — в нашей
Политике обработки персональных данных.